Monday, February 3, 2020

የሲኦል አረቄ ጠማቂዎች ማህበር😘 ምዕራፍ 1 ✍️ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ . . . የሲኦል አረቄ ጠማቂዎች ማህበር እ.ኤ.አ 2004 ዓ.ም ጥር 8 ቀን በኢትዬጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ሸራተን አዲስ መኝታ ክፍል በሁለት ግለሰቦች ጠንሳሽነት የተመሰረተ ማህበር ነው፡፡

የሲኦል አረቄ ጠማቂዎች ማህበር😘

ምዕራፍ 1

✍️ደራሲ ዘሪሁን ገመቹ
.Image result for areke ethiopian drink"
.
.
የሲኦል አረቄ ጠማቂዎች ማህበር እ.ኤ.አ 2004 ዓ.ም ጥር 8
ቀን በኢትዬጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ሸራተን አዲስ መኝታ
ክፍል በሁለት ግለሰቦች ጠንሳሽነት የተመሰረተ ማህበር ነው፡፡
ማህበሩ በአሁኑ ጊዜ ያሉትን አባላት ከተላያየ የአለም ጥግ እና
የኢትዬጵያ ክፍል በማሰባሰብ እንዲህ ያለውን ቅርጽ እንዲይዝ
ለማድረግ የሁለት ዓመት ተኩል እልክ አስጨራሽ ትግል እና
ረብጣ የሚባል ዶላር ፈጅቶበታል፡፡
ከዚህ ማህበር ሁለቱ ፈጣሪዎች ውስጥ አንዱ ሻምበል ያሲን
ሁሴን ሲሆን ሌለኛው ግን የማይታወቀው ወይም ስውሩ ሰው
በመባል የሚታወቀው ሰው ነው፡፡ይህን ስውር ሰው ከሻምበሉ
ውጭ ማንም አይቶት ወይም በማንኛውም የመገናኛ ዘዴ አናግሮት
አያውቅም፡፡የዚህ ስውር ሰው እና የሻምበሉ ግንኙነት በኦሪት ጊዜ
የነበረውን የሙሴን እና የእግዚያብሄርን አይነት ግንኙነት ነው፡፡በዛን
ዘመን ህዝበ እስራኤልና ከግብፅ ባርነት ከፈርኦን አገዛዝት
ለማውጣት እና ወደ ተስፋይቱ ምድር ለማድረስ በነበረው ውጣ
ውረድ የሁሉ ነገር ዕቅድ ነዳፊ መንገድ ቀያሽ ስውሩ እግዚያብሄር
ሲሆን ይሄ ስውሩ እግዚያብሄር ግን ለህዝብ ግልፅ ለሆነው ሙሴ
ብቻ በአካል በመታየት ዕቅዱን ያስረዳዋል …ትዕዛዙን ያስተላልፈል
ሙሴ ደግሞ ትዕዛዙን ወደ ህዝቡ በማውረድ ተፈጻሚ ያደርግ
ነበር፡፡እንግዲህ ለዚህ ማህበር ሻምበሉ ልክ እንደ ሙሴ ነው
ልንለው እንችላለን፡፡በስውሩ ሰው ሙሉ ስልጣን የተሰጠው
ፈላጭ ቆራጭ ግለሰብ ነው፡፡አንዳንድ ተጠራጣሪ የሆኑ የማህበሩ
አባለት እንደውም ስውሩ ሰው የሚባል አካል የለም ፤የሁሉ ነገር
መነሻማ መድረሻማ እራሱ ሻምበሉ ነው ይላሉ ፡፡ስውሩ ሰው
የተባለው የፈጠራ ሰው እኛን ለማደናገር የተፈጠረ ነው ይላሉ፡፡
በአጠቃላይ በሁለት ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ተሰርቶ ያለቀው
የሲኦል አረቄ ጠማቂዎች ማህበር ጠቅላላ መዋቅር
እንደሚከተለው ነው፡፡
1የሲኦል ፈጣሪ
ይሄ የስውሩ ሰው ልዩ መጠሪያ ወይም የኮድ ስም ነው፡፡
የማህበሩ ከፍተኛ ስልጣን በእጁ ይገኛል፡፡ከእሱ አንደበት
የመነጨ ማንኛውም ትዕዛዝ በማህበሩ ውስጥ ያለምንም
ማመንታት እንደወረደ ይተገበራል፡፡ስውር ቢሆንም መንፈሱ
በእያንዳንዱ አባላት አዕምሮ ውስጥ ከፈጣሪያችው እኩል
ለአንዳንዱም ከዛ በላይ ሰርጾ ገብቷል፡፡ሁሉም የማህበሩ አባላት
የማህበሩ ዋና አላማ ከግብ ካደረሱ ቡኃላ ካለበት በመውጣት
ለተከታዬቹ ይገለጽ ይሆናል…አብሮን ማዕድ ይቆርስ ይሆናል…
በማለት ተስፋ ያደርጋሉ፡፡
2ሳጥናኤሉ
ይሄ የማህበሩ ሁለታኛ ሰው ሻምበሉ ነው፡፡በማህበሩ በትክክለኛ
ስሙ በሁሉም የሚታወቅ ብቸኛው ሰው ነው፡፡ይሄ ሳጥናኤል
የማህበሩ ሞተር ነው፡፡ከሲኦል ፈጣሪው የሚደርሰውን ቀጭን
ትዕዛዝ ይሄን አድርግ….ይሄን ገንባ… ይሄን አፍርስ የሚል ጥቅል
ትዕዛዝ ዕቅድ ነድፎ..የአፈጻፀም መመሪያ ቀይሶ ..ለአባላቱ ለእዛ
ሚመጥን ልዩ ስልጠና እንዲያገኙ ሁኔታዎቹን አመቻችቶ ውጤት
ለማግኘት ሙሉ ሀላፊነት ያለመታከት በጫንቃው በመሸከም
ሁሉንም ዕቅድ ተግባራዊ የሚያደርግ በማህበሩ የሚዳሰሰው
አማላክ ነው፡፡ይህ ሻምበል የደርግ ልዩ አየር ወለድ ነበር፡፡በዛኑ
ዘመን ለሶስት አመት ልዩ ወታደራዊ ስልጠና ከራሺያ ወስዶል፡፡
ከአስር አመት በላይ የሻዌ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ጣቢያ የስላጠና
ዘርፍ ኃላፊ በመሆን አገልግሎል፡፡ሻዌ ማሰልጠኛ ጣቢያ በባሌ ዞን
ከደሎ መና ከተማ በሃያ ኪ.ሜ እርቆ ሀረና ጫካ ውስጥ የሚገኝ
በደርግ ጊዜ የሀገሪቱ ወታደራዊ ማሰላጠኛ ጣቢያ የነበር ካምፕ
ነው፡፡ በዚህ ቦታ ከሃያ ዓመት ዘረፋ የተረፍ አንዳንድ ቅሪቶቹ
በቦታው ይገኛሉ ፡፡አሁን ደግሞ የሲኦል አረቄ ጠማቂዎች ማህበር
ምሽግ ሆኖል ፡፡የዚህ ሳጥናኤል ታሪክ ከደርግ መንኰታኮት ጋር
አብሮ የተንኰታኮተ ቢመስልም በኢትዬ ኤርትራ ጦርነት ጊዜ
ኢህአዲግ የደርግ ከፍተኛ መኮንኖችን እና የጦር አዛዦችን
ከያሉበት ስርቻ ውዝፍ ደሞዛቸውን እየከፈለ ጦርነቱን በዕውቀት
እንዲያግዙት ከራሱ ጦር ጋር ሲቀላቅላቸው ዳግም የመቀላቀል
ዕድል ገጠመው፡፡ሌላ የህይወት ምዕራፍ ፡፡ከጦርነቱም ቡኃላ
በአገሪቱ የተወካዬች ምክር ቤት በአዋጅ እንዲቋቋም ተደርጎ
በነበረው የአገሪቱ ፈንጅ አምካኝ ቡድን ውስጥ ተሳትፎ
ነበረው..ቡኃላም ብዙ ብዙ ታሪክ አለው…..
አሁን ዕድሜው ስልሳ ሁለት የደፈነ ሲሆን አካላዊ ይዞታው ወደ
አርባ ሁለት አመት ዝቅ ተደርጎ እንዲገመት ያደርገዋል፡፡ግዙፍ
ነው፡፡ዘጠና ሁለት ኪሎ ይመዝናል፡፡እንዲህ ሲባል ታዲያ
የተንዘረጠጠ ተክለቁመና አለው ማለት አይደለም.. በእስፖርት
የዳበረ ፈርጣማ እንጂ፤በዛ ላይ ቁመቱ 2.01ሜትር ነው፡፡
ማንኛውም ሰው ፊት ለፊቱ ሲቆም የማርበድበድ እና የፍራቻ
መንፈስ የመርጨት ልዩ ብቃት አለው፡፡በዛ ላይ ዘወትር ለሳቅ
የማይሸነፍ ኮስታራ ግንባር ነው የተሰጠው፡፡ተስገምጋሚ ጥርት
ያለ ድምጹም ሌላው ስጦታው ነው፡፡ይህ ሰው የአገሪቱ ኢታማዠር
ሹም ጄኔራል ሆኖ ቢሾም አገሪቱ ለጐረቤት የሚያስፈራ ጦር
መመስረት እንደምትችል አያጠራጥርም… ግርማ ሞገሱም
ችሎታውም ስላለው፡፡
ይህ ሳጥናኤል የማህበሩ ጭንቅላት እንደመሆኑ መጠን ስለእሱ
የሚነገሩ ነገሮች ይበዛሉ፡፡የሚቀርቡት ምላጭ ነው ይሉታል፡፡
ምላጭ ለዓይን የማይጥመውን ነገር አስተካክሎ ውበት
ይጨምርበታል …ያሳምራል…የረዘመውን ያሳጥራል…
የተንከረፈፈውን ከርክሞ ያስተካክላል…የረዘመውን ቆርጦ
ይጥላል፡፡በተቃራኒው ደግሞ ምላጭ ይሸረክታል… ጉሮሮ
ይበጥሳል…በእናት እና ልጀ መካከል የነበረውን የአንድነት መንፈስ
እንደቀልድ በጥሶ ይጥላል፡፡
ሳጥናኤል እንዲህ ነው፡፡በጣም ቆራጥ …የሚገርም ነገሮችን
የመፍጠር እና የማደራጀት ልዩ ችሎታ የታደለ ከአምስት በላይ
ቋንቋዎችን አቀላጥፎ መናገር የሚችል(አማርኛ
፤ኦሮሚኛ፤ትግሪኛ፤አረብኛ እና እንግሊዘኛ) ግን ደግሞ
በተቃራኒው፤ጨካኝ ፤ለዓላማው መሳካት የእናቱን ልጅም ቢሆን
ከማረድ የማያመነታ፤በጣም ተጠራጣሪ እና ተነዳፊ
ጀግና፤ሀይማኖቱ በራሱ ስሜት ብቻ ማመን የሆነ ባለ ውስብስብ
ስብዕና ባለቤት ሰው ነው፡፡
3የሳጥናኤል ሴት
ይህቺ ሴት በዋናነት የሳጥናኤሉ የጭን ገረድ ነች ፡፡ዕውቂያቸው
ዘመናት ያስቆጠረ ግን ደግሞ ለዓመታት ተቋርጦ የነበረ ይሄ
ማህበር ሲመሰረት ዳግም የተጀመረ ነው፡፡የሳጥናኤል ሴት ጠይም
መልከ መልካም ግራ ጉንጮ ላይ 8 ሣ.ሜትር ርዝመት በ2 ሚ.ሜ
ስፋት ጠባሳ የተጋደመባት፤ሳቀች ሲሎት ፊቷን የምታጨማድድ …
አጨለመች ሲሏት ውስጥን የሚያረሰርስ ደስታ የሚረጭ ሳቅ
የምትለግስ የማይጨበጥ ባህሪ ያላት የማህበሩ ወሳኝ ሰው
ነች፡፡
በግልፅ ስልጣኖን ለመናገር‹‹የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር
››ማለት ትችላላችሁ፡፡በሲኦል አረቄ ጠማቂዎች ዋና ካምፕ
ውስጥ ያሉ ጠቅላላ የውስጥ እንቅስቃሴዎች በእሷ ነው
የሚመራው፤ይሄም ሳጥናኤሉ አዕምሮው በጥቃቅን የውስጥ
ጉዳዬች እንዳይጨናነቅ እና ዋና ዋና የማህበሩ አላማዎችን ላይ
እንዲያነጣጥር እና የማሰብ ኃይሉም እንዳይበታተንበት የማይናቅ
እገዛ እያደረገችለት ነው፡፡በዛ ላይ ወታደራዊ ዕውቀቱም ልምዱም
አላት፡፡የወያኔ ታጋይ ነበረች፡፡የዛሬን አያድርገውና፡፡
4ሰይጣኖቹ
ሠይጣኖቹ በቁጥር አስር አባላት ያሉት የማህበሩ ዋና አከርካሪ
የኮድ ስም ነው፡፡አስሮቹም ቀድሞም ወታደር ነበሩ ዕድሜያቸው
ከ30-50 ውስጥ ያለ፤በአሁኑ ጊዜ አለ የተባለ ዓለም አቀፍ
ወታደራዊ ስልጠና የሰለጠኑ ለማንኛውም የማህበሩ ግዳጅ
እስከህይወት መስዋዕትነት ለመክፈል በጣም ቁርጠኞች
ከመሆናቸውም በተጨማሪ የማህበሩም ዋና አሴት ተደርገው
ይቆጠራሉ፡፡የአንድ ክፍለ ጦር ወታደር ያ

Sunday, January 19, 2020

የፒያሳዋ ወፍ ክፍል ሶስት መጨረሻ

የፒያሳዋ ወፍ    ክፍል ሶስት መጨረሻ

Image result for የፒያሳዋ ወፍ

‹‹ልጄ እናቴ ጋር እተዋታለው..ወይም እህቴ ጋር አስቀምጬያት መጣለው››

‹‹አይ እንድትመጣ አልፈልግም..ጊዜው ሲደርስ እራሴ እመጣለው››ኮስተር ብዬ

መለስኩለት ..እወነቴን ነው አሁን እዚህ እሱ መጣ ማለት እኮ ከእሱ ጋር ስንከረፈፍ

አላማዬን ሙሉ በሙሉ መዘንጋት ማለት ነው….አንዲመጣማ አልፈቅድለትም

‹‹አልፈልግም ..››አንቧረቀብኝ‹‹..ልጠብቅሽ አልችልም..ጂጂ የምትባል ሴት አላውቅም…

ፈጽሞ አይቼያትም አላውቅም..ጂጂ ቅዠት ነች..ዝም ብላ በህልሜ እየመጣች

የምትረብሸኝ መንፈስ ነች…እንዲህ ነው ማመን የምፈልገው..ስለዚህ እንዳትደውይልኝ…

ከዛሬ ጀምሮ አልፈልግም እንዳትደውይልኝ››ጠረቀመው…….ደነገጥኩ.. ፈራው ..በጣም

ፈራው…እና አልደውልለትም ማለት ነው……?ካልደወልኩለት ድምጽን ካልሰማው ምን

ሊውጠኝ ነው…?፡፡ለመሆኑ ለህይወቴ በጣም ሚያስፈልገኝ የትኛው ነው……?ሁለት ስሜቶች

ግራና ቀኝ ወጥረው ይዘውኛል..ለዋቅቶላ ያለኝ ስሜት እና ለሮማን ያለኝ ስሜት..አንዱ

የፍቅር ሌላው የበቀል(ጥላቻ)….ከበቀል እና ከፍቅር የትኛው ይጠቅማል ብዬ እራሴንም ሆነ

እናንተን አልጠይቅም..…?እንደዛ ብዬ ብጠይቅም የዋህነት ነው የሚሆነው..ትክክለኛው

ጥያቄ መሆን ያለበት ከፍቅርና ከበቀል የትኛው የበለጠ ኃያል ነው…? የሚል መሆን

አለበት…የትኛው ነው ይበልጥ አዕምሮን የሚበላው..…?የትኛው ነው ልብን የሚፍቀው..…?

የትኛው ይበልጥ የሚያቃትተው…?ያው ሁለቱም ስሜት በውስጤ ይገኛሉ.. የትኛው ነው

ባለድሉ….…?

ሁሉን ነገር አገናዝቤ ለመብርር ወሰንኩ.. ልሄድ …..ወቅቶላ ማረኝ ..ሁለተኛ አላበሳጭህም

ልለው..ሁለተኛ ጥዬህ ከስርህ አልሄድም ልለው…ወንድም ሁነኝ ልለው…ልብሴን ሁሉ

ሰበሰብኩ ሸንጣዬንም አዘጋጀው..በራሴ ሚኒባስ ልበር… አዎ ሹፌሩ ጋር ልደውል ቁጥሮቹን

መነካካት ጀመርኩ….ከመጥራቱ በፊት የቀጠርኮቸው ጓደኞቼ ጫታቸውን ተሸክመው

እየተንጋጉ ወደ ክፍሌ ሲገቡ ነው ስልኩን ያቆረጥኩት..ለካ ቀጥሬቸዋለው… እንደምንም

እራሴን አረጋግቼ ሁሉን ነገር ትቼ አብሬቸው ቁጭ ብዬ መቃም ጀመርኩ…

አሁን ቢያንስ ከተቀመጥን አንድ ሰዓት አልፎናል..መቃም ከጀመርን..እንሱ እንደተቀመጡት

የተቀመጥኩ እንሱ እንደሚቅሙት እየቃምኩ ቢሆንም ሀሳቤን ግን እንደነጋርኮችው

መሰብስብ ተስኖኛል…የልብ መሸፈት ለካ እንዲህ ከባድ ነው..

‹‹አሁን ስለ ዕቅዳችን መነጋገር ብንጀመር ምን ይመስልሻል…?››ስንዝሮ ነው ድንገት

ፀጥታውን ያደፈርሰው

‹‹ምን አልከኝ..…?ምን ……?ዕቅድ››ድንግርግሬ ወጣ

‹‹አዎ ..እንዴት እንድናደርግ ነው የምትፈልጊው .. …?እንድንገድላት ነው..እንግደላት

አይደል…?››አለኝ ምንም ማወላወል ሳይታይበት..በነገራችን ላይ እኚ ጎደኞቼ ስለ እኔ እና

ሮማን ታሪክ ጫፍ ድረስ ያውቃሉ..እኔ በምጠላትም መጠን ይጠሏታል…የእሷን አንገት

መቀንጠስ ለእነሱ የዶሮ አንገት የመቀንጠስ ያህል አያሳስባቸውም

የእሱ ንግግር ግን እኔን ወደ ቀልቤ መለሰኝ ተንሳፎ አየሩን ሰንጥቆ በመብረር ዋቅቶላ ጉያ

ሊወሸቅ ሲያኮበኩብ የነበረው ልቤን መንጭቆ በመመለስ ከቀልቤ እንድሆነ

አደረገኝ..በመጠኑም ቢሆን ማለቴ ነው…

ግን ቅድም ልሄድ የወሰንኩት ምን ነክቶኝ ነበር……?..የምን መልፈስፈስ ነው……?እሱ

ከተልፈሰፈሰ እኔም አብሬው መልፈስፈስ አለብኝ እንዴ..…?ለዛውስ እሱ እንዲህ የሚሆነው

ምን አልባት ፍቅር ይዞት ሊሆን ይችላል..…?አዎ ወንዶች መቼስ ወደ በፍቅር ባህር ውስጥ

ለማዋኘት ዘሎ በመግባትም እና ለሰከንዶች ተንቦራጭቀው ለመውጣት ሚቀድማቸው

የለም…እኔ ግን አላፈቀርኩት…እንዲሁ ደስ ሰለሚለኝ እንጂ ፍቅር አልያዘኝ…ትንሽም ቢሆን

ያው ሶስት ቀን አብሬው ስለዋልኩና ስለደርኩ ለምጄው ይሆናል ይቺ ታህል ልቤ

የምትዋልለው…አዎ …እርግጠኛ ነኝ ፡፡…ዋል አደር ስል ደግሞ ስለእሱ ማሰብና መጨነቅ

አቆማለው..አረ ጭራሽ እረሳዋለው…እወነቴን ነው ….፡፡

ስለዚህ አሁን ወደ አላማዬ ልመለስ… ትኩረቴን ልሰብስብ….እራሴን ለማሳመን

ያልቀባጠርኩት ነገር የለም…ለካ እራስን እንደማሳመን ከባድ ነገር የለም…ልብ ካልመሰለው

የአዕምሮ ሰበካ የቁራ ጩኃት ነው የሚሆንበት ..

‹‹እኔ ነኝ የምገድላት …በጣም እኮ ነው የምታስጠላኝ…››ኩለሻ ነች የፎከረችው

‹‹ኩኩሻዬ ፍቅር… አኔ እያለወልሽ አንቺ ምን በወጣሽ በዚህች ዳቢሎስ ደም ይሄንን

የመሰለ አለንጋ ጣትሽን ታቆሺሻለሽ....ለእሳ እኔ አለውላት››ስንዝሮ ተቃወማት..

‹‹ሁለታችሁም አትቸገሩ ..አኔ ነኝ አንገቷን ፈጥርቄ እስትንፋሶን የማቋርጠው››ዋርካው

ተናገረ…በግማሽ ልቤ እያደማጥኮቸው ነው…ይሄ የዘወትር ጭቅጭቃቸው ነው..እንዲህ

አይነት ለአደጋ መጋፈጥን የሚጠይቅ ስራ ሲኖረን እንዲሁ ናቸው..እኔ ቀድማለው..እኔ ነኝ

ምቀድመው..ለእኔ ተውሉኝ ለእኔ….አዎ ዝም ብላቸው ለአንድ ሰአት ይጨቃጨቃሉ…

ከጭቅጭቅም አልፈው ሊደባደቡ ሁሉ ይችላሉ..ይሄ ግን ለታሪክ ሽሚያ የሚያደርጉት

አይደለም..እንዲህ ገደልኩት..እንዲህ ጣልኩት ብሎ በማውራት ጀግና ለመሰኘት እና

ለመጎረር አይደለም…እርግጥ ከላይ ከላይ ለሚያዳምጣቸው ሰው እንደዛ ነው

ሚመስለው..ግን ሁሉም ሌለኛን ለመጠበቅ የሚያደርጉት ከቀናነት እና ከአሳቢነት የመነጨ ሚስጥራዊ ደባ ነው...አደጋ ካለ ከእናንተ በፊት ልቅደም እያሉ ነው...ሞት ሲመጣ ሶስቱም ምርጫቸው እድለኛ ሆኖ መትረፍ አይደለም..ከሶስት አንዱ መሞት የግድ ከሆነ ቀድሞ ለመሞት ነው የሚራኮቱት...እራስን  ለሞት አሳልፎ በመሥጠት ለተቀሩት ሁለቱ ህይወትን ለመስጠት ..እስርምሰ ሲመጣ እንደዛው ነው በራስ ላይ መስክሮ ሌላው ነፃ ማውጣት..ግን

ብዙውን ጊዜ ሶስቱም ቦሊስ እጅ ሲገቡ ሶስቱም እኔ ብቻዬን ነው ያተፋውት እነሱመምንም

አያውቁ ስለሚሉ ለፖሊስ ምርመራ ጣም ያስቸግራሉ…...እኔም ለዚህም ነው

የምወዳቸው..ለዚህም ነው በማንኛውም የሰው ልጅ ሕይወት የማልቀናውን በእነሱ

ምቀናባቸው… በምንም ላይ ባልተመረኮዘ እወነተኛ ንጽህ ፍቅራቸው…

…….ቆይ አንዴ ስልኬ ጮኸ …ማለቴ ሚሴጅ ገባልኝ.. እየጠበቅኩ ያለውት ነገር እንዳለ

ሁሉ አፈፍ አድርጌ አንስቼ ከፈትኩት..በምርቃናው ላይ ድንጋጤ አንቀጠቀጠኝ… ላብ

በአፍንጫ ቸፍ አለ..ምክንቱም የመጣው መልዕክት ከጠበቅኩት ቦታ ነው….ከዋቅቶላ..

‹‹ይቅርታ ቅድም አትደውይልኝ ያልኩሽ ስለናፈቅሺኝ ነው…እንዴ ካልደወልሺልኝማ

አብዳለው››ይላል…

አሁን ፈገግ አልኩ….እንደውም ስሬ ያሉትን ጓደኞቼ ይፎግሩኛል ብዬ ሼም ይዞኝ እንጂ

ተንከትክቼ መሳቅ ነበር ያሰኘኝ…ልቤ ላይ ተቋጥሮ የነበረና መተንፈስ ሁሉ ከልክሎኝ የቆየው

ቆጥኝ ነገር ደማሚት እንደተለኮሰበት አለት ፈንድቶ ሲበታተን ታወቀኝ…

.‹‹ አትደውይልኝ ብትልም መደወሌን አላቆምም ነበር..››ብዬ መለስኩለት..ግን ከዚህ በላይ

ብዙ ብዙ ነገር ነበር ልለው የደፈለግኩት..ግን ምን እለዋለው..…?ያው ጥሩ ጓደኛዬ

ስለሆንክ…አይ እንደዛ አይደለም የምለው..ወንድሜን ስለምትመስለኝ

ትናፍቀኛለህ….የትኛው ወንድሜን..…? (እናቴ በህይወት ቆይታ ቢሆን ኖሮ ምን አልባት

ትወልድልኝ የነበረውን) .. ያሰብኩት ሁሉ ስሜቴን በሙላት የሚገልፀልኝ ስላልሆነ ጽፌ

ላስተላልፍለት አልችልም…ስሜቴን በሙላት የሚገልጽልኝ ታዲያ ምን ብል ነው..…?ያንንማ

እኔ ራሴ የት አውቀውና ..ብቻ አንድ የሚረብሽ ነገር ዝም ብሎ ይተናነቀኛል…በአዕምሪዬ

ይጉላላል በስሜቴ ተዳፍኖ ያብሰለስለኛል…

..ወደ ጓደኖቼ ተመለስኩ‹‹ጭቅጭቃችሁን አቁሙ..››ፀጥ አሉ

‹‹እንድንገላት አይደለም የምፈልገው..ለመግደልመ እኔ ዛሬ ለሊቱኑ ፀት

አደርጋታለው….እናንተም አታስፈልጉኝም ነበር..፡፡የምፈልገው….እንድናሰቃያት ነው.እርግጥ

መጨረሻ ላይ እንድትገደል እፈልጋለው…፡፡ያንን ጊዜው ሲደርስ እራሴው የማደርገው ይሆናል

…አሁን ግን የእናንተን እገዛ ምፈልገው በቁም ነፍሷ በውስጧ እያለ የቁም ሞት

እንድንገድላት ነው..ፃረ ሞት እንድንሆንባት…እያንዳንዶን የሰራቻትን ሰይጣናዊ ድርጊት

እያሰበች በፀፀት እንድታጣጥር…ሞቷን እንድትለምን..ግደሉኝ ብላ እንድትማፀነን…

እያንዳንዱን በግፍ የሰበሰበቻትን ንብረቷን አጥታ ደቦ መግዛዣ እንድታጣ…መንገድ ላይ

ወጥታ እንድትለምን..

‹‹እንዴ የአሜሪካ አክሺን ፊልም አደረግሺብን….››አለኝ ያ ተንኮለኛው ሲንዝሮ

‹‹እንዴት…?››ምን ለማለት ፈልጎ እንደሆነ ስላልገባኝ ጠየቅኩት

‹‹ንብረቷን መቀማት..እሷን ለማኝ ማድረግ… ማስራብ… ማሳበድ..በስንት ጊዜ ውስጥ ነው

የምናደርገው››

‹‹መጀመሪያ ስድስት ወር ነበር የመደብኩላት..አሁን ግን ጊዜ የለኝም..በአንድ ወር ውስጥ

የአለምን ስቃይ ሁሉ ማየት አለባት..››

‹‹አንድ ወር..ምነው እንዲህ ቸኮልሽ…?››ኩኩሻ ነች የጠየቀቺኝ

‹‹ጌዜ የለኝም…ከዚህ አገር ልመርሽ አስቤያለው››

ሶስቱም ክው ብለው ደነገጡ…በተለይ ዋርካው ያን ፊቱን አጨማዶ ለንቦጩን ሲጥለው…

የሆነ የህጻናት ማሰፈራሪያ መሰለ

‹‹አይዞችሁ..እኔም እንዲህ አላዘንኩ››

አረ የመጬ አይነፋም..አንቺ እኮ የፒያሳ ልጅ ነሽ ፓሪስ ብትሄጂ እንኳን አትለምጂም››

‹‹አታስቢ …ገና እርግጠኛ ሆኜ አልወሰንኩም..ግን በቃ አንደ ወር ከተሰቃየችና ሞቷን

ካስመኘናት ይበቃል..ከዛ እኔ አጠናቅቃታለው…፡፡ማጠናቀቂያው ላይ እናንተን

አልፈልጋችሁም… ብቻዬን ነው የማደርገው…ፈረሰኛው ጊዬርጊስ ካላጋለጠኝ አሪፍ ነው…

ካልሆነም ዕቅዴ ይሳካ እንጂ ጋማ ብባልም ጣጣ የለውም ..ያው አንድ ሃያ አመት ጠጥቼ

ሼባ ሆኜ ስወጣ እንገናኛለን››

…ዋርካውን ደረት ላይ ተደግፋ ስንዝሮን ጡቶቾ መካከል አስደግፋ …‹‹አረ አይነፋም››አለች

ኩኩሻ አሁንም ደግማ።።ቀኑን ሙሉ ተኝቼ ነው የዋልኩት፡፡ይሄን ያደረግኩት ዛሬ ለሊት የመተኛት ዕድሉ ስለማይኖረኝ

ጥሩ እረፍት ለመውሰድ ነው፡፡ከእንቅልፌ ስነቃ 11 ሰዓት ነበር፡፡ዛሬ ለእኔ ልዬ ቀን ነች፡፡

ታላቅ ተግባር የማከናውንበት ቀን ….፡፡ከዛ በፊት ግን ዘና ማለት አለብኝ፡፡አዎ መንፈሴን

ንጽህ እና በጥራት የሚያስብ መሆን አለበት….ለዚህም ይረዳኝ ዘንድ ጋሼ ዜናን ከቤት

ይዣቸው ወጥቼያለው..፡፡ለእኔ ምሳዬን ለጋሼ ደግሞ እራታቸውን አብረን ከበላን ቡኃላ

በአሁኑ ሰዓት ምግብ ቤቱን ለቀን አንድ አነስተኛ ካፊ በረንዳ ላይ ተቀምጠን የሆድ

የሆዳችንን እያወራን እግረ መንገዳችንን ወጪ ወራጁን እየተመለከትን እንገኛለን….

ብዙ ብዙ ወሬ ካወራን ቡኃላ ድንገት ያስደነገጠኝን ጥያቄ ጠየቁኝ‹‹‹ሰውዬሽ ደህና ነው…?››

‹‹የቱ ሰውዬ…?››

‹‹ያ ለሶስት ቀን ጠልፎሽ የነበረው…ነዋ››

‹‹እ!!! እሱን ነው……?እኔ እንጃ ሰላም መሰለኝ…ያው ጠልፎ ከመለሰኝ ወዲህ መች

አገኘውት..…?››

‹‹ጠልፎ ከመለሰኝ አልሽ .. …?››አሉኝ …በዛ የተለመደ ማሽሟጠጣቸው፡፡

‹‹አዎ ጠልፎ ከመለሰኝ..!!!››ምንም እንዳይሉኝ የፈራው በሚመስል የጠነከረ ንግግር

ግግም ብዬ

‹‹ምኑን መለሰሽ… አሁንም እኮ እሱ ጋር ነው ያለሺው››

‹‹ምን ማለት ነው ጋሼ ……?አልገባኝም…?››

‹‹አይ የእኔ ልጅ..አንቺ ስለ አካል መጠለፍ ነው የምታወሪው ..የአካል መጠለፍ ብዙም

አያሳስብ የልብ መጠለፍ ነው ከባዱ….አንድን ሰው የሆነ ቤት ውስጥ ከርችመሽበት

አሰርኩት ትይ ይሆናል.. ግን እውነታው እንደዛ አይደለም..እስር ቤት ከተሸ ቆለፍሽበት

ማለት ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ ከለከልሺው ብቻ ማለት ነው…እውነተኛው እስር

በመንፈስም ስትታሰሪ ነው…በስነልቦና ስትሸነፊ ነው…፡፡

.ለምን ይመስልሻል አንዳንድ ሰዎች በተለይ የነፃነት ታጋዬች አስር ወይም ሃያ አመት አንድ

ጠባብ ክፍል ውስጥ ተከርችሞባቸው ከኖሩ ቡኃላ ሲለቀቁ…ስብርብር ብለው ፤ተስፋ

ቆርጠው እና አንገት ደፍተው እናያቸዋለን ብለን ስንጠብቅ ጭራሽ በተቃራኒው አንገታቸውን

ቀና አድርገው ደረታቸውን ነፍተው ይበልጥ ገዝፈውና አስፈሪ ሆነው የሚወጡት…አካላቸውን

እንጂ መንፈሳቸው እንዲታሰር ለማንም ስለማይፈቅድ ነው…እጃቸውን እንጂ ልባቸውን

ለእስር አሳልፈው ስላማይሰጡ ነው፡፡

‹‹ጋሼ ጫወታህን ያው እንደልማድህ ፖለቲካዊ አደረግከው እኮ..››አልኩት ወደ አጀንዳው

ልመልሰው ስለፈለኩ

‹‹አይ ምሳሌ ልስጥሽ ብዬ ነው..አንቺ አካልሽን ከተጠለፍሺበት አስለቅቀሽ መጥተሸል

እናም በዛ እየተኩራራሽ ነው....ልብሽ ግን አሁንም እንደተጠለፈ ነው..ደግሞ ሳስበው

እንዲህ በቀላሉ የምታስመልስ አይመስለኝም፡፡

‹‹እንዴ ጋሼ አሁንም አልገባኝም…?››

‹‹ለመሆኑ ስሙ ማነው..…?››

‹‹ዋቅቶላ ይባላል…ወይኔ…ማለቴ የትኛ ሰውዬ…?›› ዘበራረቅኩ

‹‹የትኛው ሰውዬ አልሽኝ..…?ነገርሺኝ እኮ …ዋቅቶላ ብለሽ ነገርሺኝ…አዕምሮሽን የሞላው

ስም እሱ ነው…ደውለሺለት ታውቂያለሽ…?››

‹‹አዎ አንተን ከማግኘቴ በፊት ደውዬለት ነበር…ተወው ባክህ እሱ ነጭናጫ ነገር ነው…››

‹‹ነጭናጫ አልሽ..…?ፍቅር ሲይዝ እኮ እንደዛ ነው የሚያደርገወ ያነጫንጫል…››

ይሄንን አይነት ወሬ በዚህ ወቅት አልፈለግኩም..ይሄ ጫወታ ወደ ትካዜ የሚጨምረኝ እንጂ

ፈታ የሚያድገኝ አይደለም…የሚያልፈሰፍሰኝ እንጂ ጥንካሬ የሚያላብሰኝ አይነት ጫወታ

አይደለም..እና ጫወታውን ወደ ሌላ አቅጣጫ ለወጥኩት

ጋሼ እነዛን ፍቅረኛሞች አየሀቸው… እሷ እኮ እየለመነችው ነው ..እሱ ደግሞ

ይንጠባረርባታል…እንዲህ አይነት ወንዶች ያባሳጩኛል…

ፊት ለፊትችን እየተጨቃጨቁ ስለሚሄዱ ሁለት አፍላ ወጣቶች ነው የማወራው..ልጁ

ቀጫጫ ..ባለደበሌ ፀጉር..ግን ደግሞ ቆንጆ ነው…ዘመንኛ አለባበስ የለበሰ ሱሪው

በማጥለቅ እና በመውለቅ መካከል የሚዋልል የሚመስል..ላድርገው ወይስ ላውልቀው

እያለ ከራሱ ጋር ሲሞገት ቆይቶ መወሰን አቅቶት ሱሪው ባለበት መሀከል ቦታ ላይ ጥሎት

የወጣ የሚመስል…እሷ ፍቅረኛው…ለዕርቃን የተጠጋ አለባባስ ለበሰች…ከሰር ያጠለቀቻት

ብጣቂ ቀሚስ በብስጨት እንጣጥ እንጣት ስትል ንፋሱ ወደላይ ሲያነሳት ከስር

ያጠለቀችው ነጭ ፓንት በቀላሉ የሚታይ ..ከላይ የሁለቱ ቱቶቾ ሰማኒያ ፐርሰንት ግዛታቸው

ለእይታም ለንፋስም የተጋለጠ አለባበስ የለበሰች ነች፡፡

‹‹ምነው ተፈቅረህ አታውቅም እንዴ..…?አንተን በየሄድክበት እየተከተልኩ መለመን

አለብኝ…?››እየተንዘረዘረች ትጮህበታለች፡፡

እኔ ለምኚኝ አላልኩም ..ግን መጨናነቅ አልፈልግም …ትንፋሽ አሳጣሺኝ››ይላታል..በተ

ንገሸገሸ ስሜት….

እንደዛው እየተነጋገሩ አልፈውን ሄዱ…

የጋሼን የወሬ አቅጣጫ መለወጥ ተሳካልኝ…ግን በራሱ መንገድ ነው ያየው…

የእኔ ወፍ አየሽ ዘመን ብዙ ነገር ይቀይራል፡፡ወንድነትም ተቀይሯል… የእኛ ጊዜ ወንድ

የሚበላው ጮማ ስጋ … የሚጠጣው ደግሞ ንፅህ የማር ጠጅ ነበር…እንዲህ ስልሽ

በውስጥሽ ጥያቄ መፈጠሩ አይቀርም…ምክንያቱም ጮማውም አለ ጠጁም ቁም ነገሬ ብሎ

የሚጠጣው ሰው ባይኖርም አሁንም አለ ብለሽ ታስቢ ይሆናል… አዎ ትክክል ነሽ እኔም

መኖሩን አውቃለው …ግን ከእኛ ዘመን ጮማ ጋር ምኑም አይገናኝም ፡፡የአሁኑ ማለቴ

የእናንተ ዘመን የውሸት ነው፡፡በመድሀኒት የወፈረ አርቴፊሻል ጮማ እና ልብን የሚፍቅ

የስኳር ስሪት ጠጅ ነው ያለው፡፡

በተጨማሪም የአሁኑ ወንድ ሱስ አድክሞታል፡፡የሀሺሽ ሱስ …የጫት ሱስ …የገንዘብ

ሱስ..የፌስ ቡክ ሱስ..የመኪና ሱስ ….የቴክኖሎጂ ሱስ ….በቃ ሱስ በሱስ….. ስለዚህ

ለሴት የሚኖረው ፍላጎት ከእነዚህ ሁሉ ፍላጎቶች የተረፈ ሸርፍራፊ ስሜት ነው..ያቺ ሽርፍራፊ

ስሜትን ለመቀስቀስ ደግሞ እንዲህ እንደምታያት ብጣቂ ልብስ ለብሳ ማስታወስ እና

መፈታተን ከሴቲቱ ይጠበቃል..ለዛውም ከገባው…፡፡ቴዲ አፍሮ በቅርቡ የለቀቀውን

የሰብልዬን ክሊፒ አይተሸል…በዛብህ የሚማልለው የሰብለን ቁርጭምጭሚት እያየ ነው…

ሙሉ ያልተበታተነ ልብ ያለው አፍቃሪ ወንድ የሴት የፍቅረኛውን የእግር ኮቴ በጨረፋታ

ማየት እንኳን ወንድነቱን ይረብሸዋል…ውስጣዊ ስሜቱን ይነቀንቅበታል….…አየሽ ልዩነቱን..››

እንግዲህ ጋሼ እንዲህ ነው… አንድ ቁራሽ ነገር ካሳዩቱ ..ያንን አንዴት ተርጉሞት ከምን ጋር

አገናኛቶት እንደሚተነትነው ሁሌ ያሰገርመኛል…በነገራችን ላይ ከእሱ ጋር ዕድሜ ልኬን

ከመኖሬ የተነሳና እሱን ማዳመጥም ሰልችቶኝ ስለማያውቅ የእሱን ባህሪ ወርሼያለው…ነገር

ማሰፋፋት እና ማወሳሰብ እየተክንኩበት ነው…ሀይስኩል እንኳን ሳረግጥ ከዩኒቨርሲቲ

ምሩቆች ጋር ደረቴን ነፋ አድርጌ በማንኛውም ርእስ ላይ እኩል የማውራት እና የመከራከር

ችሎታ ከጋሼ ያገኘውት ውርስ ነው….እሱም ይሄንን ይመሰክራል…አዕምሮሽ እኮ በሁለት

በኩል የተሳለ ምሳር ነው ይለኛል…በልጅነትሽ ተነከባክባ በቅጡ ስላላሰደገችሽ እና በበቂ

መጠን ስላላስተማረችሽ ይህቺ ሀገር አጥታሻለች››እያለ ይቆጫል…

ሁለት ሰዓት ሲሆን ለልጆቹ የሚበላ ነገር ተሸክመን ወደቤት ሄድን …ጋሼን አስገብቼ

ምግብን ለልጆቹ ሰጥቼ ተሰናብቼያቸው ልወጣ ስል‹‹ከእኔ ጋር አታድሪም ዛሬ…?››ብሎኝ

ብሎ ተየቀኝ

‹‹አይ ዛሬ አቤቴ ነው የማድረው››

‹‹ስራውን ትተሸል አይደል…?››ብሎ ጠየቀ…ኝ ጥርጣሬ ባረበበበት ድምፀት

‹‹የቱን ስራ…?››የትኛውን ስራ እንደጠየቀኝ በደንብ ቢገባኝም…ደንግጬ ጠየቀኩት ..ልክ

ሰርቼው እንደማላውቅ….አረ ሰርቼው ሳይሆን ሲሰሩም አይቼ።።እንደማላውቅ ነገር

ተንገሽግሼ…

‹‹አይ ዝም ብዬ ነው…በቃ ደህና እደሪልኝ

የእኔ ወፍ..አምላክ ይከተልሽ››ብሎ መረቀኝና

አሰናበተኝ

እኔም ግንባሩን ስሜ ባለው ነገር እየተነጫነጭኩ ወጥቼ ሄድኩ..እንዴ ከዋቅቶላ ጋር

ከተመለስኩ ወዲሀ ሽርሙጥና ብዬ መንገድ ላይ ወጥቼ አላውቅም..ከዛሬ ቡሃላ ይቅርብኝ

ብዬ ወስኜ አይደለም..አረ ጭራሽ አላሰብኩበትም ነበር…ግን ልክ አንደሌብቱ

ሽርሙጥናውንም ተውኩ ማለት ነው……?ወይኔ ዋቅቶላ ይሄ ሰውዬ ምን አስነካኝ .. …?

አፍቅሬው ይሆን እንዴ..…?ስለፍቅር የምታውቁ እስቲ ስሜቱ እንዴት ነው..…?አሁን እኔ

ስተዩኝ ፍቅር ይዞኛል ማለት ይቻላል……?

ይሄንን ጉዳይ አሁን ለማሰብ ጊዜው አይደለውም…ቀጥታ ወደ ቤት ነው የሄድኩት …

ለመዘጋጀት፡፡ወዲያው ነበር ሶስቱን ጓደኞቼን የጠራዋቸው…ዝግጅታችንን ሙሉ በሙሉ

አጠናቀን ከቤት የወጣነው ከለሊቱ ስምንት ሰዓት ነው፡፡

ከለሊቱ 8፡30 ሲሆን አራታችንም ሮማን መኖሪያ ቤት አቅራቢያ እንገኛለን..ሁላችንም ጥቁር

ላብስ ለብሰናል..እጆቻችን በጓንት ተሸፍኗል..ጥቁር ጭንብል ጭንቅላታችንን ሙሉ ፊታችንን

ሸፍነናል፡፡

…ይሄ መኖሪያ ቤት 1.7 ሚሊዬን ብር ነው የተገዛው…ከዚህ ውስጥ እርግጠኛ ሆኜ

የምነግራችሁ ሰማንያ ፐርሰንቱ የእኔ ንብረት ነው…የእኔ አልኩ እንዴ ……?ይቅርታ ተሳስቼ

ነው የእኔ ካልኩት ውስጥ ቢያንስ ዘጠና ፐርሰንቱ የእኔ አይደለም..የእሷም አይደለም….ያው

የሰፊው የአዲስ አበባ ህዝብ ነው…በእኔ አማካይነት ከሰፊው ህዝብ የተሰበሰበ የተዘረፈ

ማለትም ትችላላችሁ ብር ነው፡፡

…የተቀረው ደግሞ ስጋዬን ሸጬ የሰበሰብኩት ነው…ግን ስጋ መሸጥ ምን ማለት ነው ..

…? ግብረ ስጋስ የሚባለውስ ለምንድነው..…?አዎ አሁን ገብቶኛል ግብረ- ስጋ ማለት የስጋ

ብቻ ስራ ማለት ነው..፡፡አይደል……?አንድ ስጋ ከሌላ ስጋ ጋር የሚያደርጉት ግንኙነት ማለት

ነው…ፈቅር አልባ ወሲባዊ ግንኙነት፡፡

በፍቅር ውስጥ ያለ ወሲብ ግን ግብረ ስጋ ሲባል ትክክል አይደለም…ምክንያቱም በእወነተኛ

የፍቅር ተጣማሪዎች መካከል የሚደረግ ግንኙነት ስጋ ከስጋ ብቻ በማፋተግ የሚከወን

ሳይሆን የመንፈስም ቁርኝቱ የሚገዝፍበት በግንኙነታቸው ሰከንድ ሰማየ-ሰማያት

የሚንሳፈፉበት ..ከሰው በላይ የሚሆኑበት.. ከፕላኔቶች ጋር በስምም በጸሀይ ዙሪያ

የሚተሙበት ቅዱስ ክስተት ይሆናል..ይሄንን ታዲያ ግብረ ስጋ ማለት ትክክል

አይመስለኝም..እኔ በዛ መልክ አጣጥሜው ባለውቅም እንዲሁ ሳስበው ነገሩን ዝቅ

ማድረግ ይመስለኛል ..

….ወይ የእኔ ነገር አሁን እኮ ለከባድ ተልዕኮ ጓደኞቼን ይዤ አደገኛ ቦታ ነው ያለውት…

ታዲያ ስለዚህ አይነቱ ጉዳይ ምን አሳሰብኝ……?ለማንኛውም ጊቢ ውስጥ ገብተናል …

ጊቢወ ውስጥ ለመግባት ያን ያህል ከባድ አልነበረም …ዘበኛ የለውም..ወሻ

አልታሰረበትም…፡፡አጥሩም ያን ያህል አስቸጋሪ የሚባል አልነበረም…..በዛ ላይ እዚህ ጊቢ

ውስጥ ከአንድ አመት በላይ ኖሬበታለው...መግቢያ እና መውጫውን በደንብ አውቃለው፡፡

ለዚህ ለዛሬው ተልዕኮ ከሳምንት በላይ ተዘጋጅተንበታል፡፡መጀመሪያ ስለዝግጅታችን

ከመናገሬ በፊት ስለቤቱ ልንገራችሁ…ባለአራት ክፍል መለስተኛ ቢላ ዋና ቤት እና ከጀርባ

ሶስት ክፍል ያላቸው ሰርቢስ ቤቶች አሉበት…፡፡ሶስቱን ክፍል ሰርቢስ ቤት አንድ ላይ

በማቀላቀል የሚትኖርበት ሮማን ነች..የእኔዋ ደመኛ ሮማን…አብረዋት አንድ ሚስኪን ሰራተኛ

እና አንድ ጥቁር ድመት ይኖራሉ….፡፡

ትልቁ ቤትን በወር ዘጠኝ ሺ ብር አከራይታው ነበር..ተከራዬቹ ከአራት ቀን በፊት ነው

የለቀቁት..የቤቱን ኪራይ በስድስት ወር አንዴ ነበር የሚከፍሉት…. ከአራት ቀን በፊት ሲለቁ

ተከፍሎ ያልተኖረበት የሶስት ወር ኪራይ ነበራቸው፡፡

…ድንገት ልንለቅ ነው ሲሏት… ‹‹ለምን…?›› እንኳን አላለቻቸውም

.‹‹ሂሳብ መልሺልኝ አትበሉኝ እንጂ መብታችሁ ነው››ነበር ያለቻቸው….ምርጫ

አልነበራቸውም ብሩን ጥለው ለቀቁ…..

እኚህን ተከራዬች ለማስለቀቅ እኛ የሰራነው ስራ ከፍተኛ ነበር…ስንዝሮ እና ዝግባው የቤቱ

አባ ወራን መግቢያ መውጫ ተከታተሉት ….ድክመቱን ለማግኘት….ሚስጥሩን ለማግኘት

..፡፡ብዙም ሳይለፉ እጃቸው ላይ ወደቀ….ከሁለት ልጆቹ እናት ደብቆ ሹልክ እያለ

የሚሄድባት ሌላ ውሽማ አለችው…እንደሚስት ተከራይቶ ያሰቀመጣት ውሽማ…ይሄንን

እንቅስቃሴ ለሁለት ቀን እየተከታተሉ በቪዲዬ የተደገፈ መረጃ ሰበሰቡበት…

ከዛማ አለፍ ብለው ሰውዬው ባሌለበት ውሽማዋን ቀርበው ያነጋገሯታል፡፡ከዛም ጠቃሚ

ነገር ያገኛሉ ፡፡ውሽሚት ውሽማ መሆኗን አታውቅም ነበር…፡፡እጮኛ እንደሆነች…እሷን

በቅርብ እንደሚያገባት..ከእናቱ እና ከእህቱ ጋር እንደሚኖር…እህቱ ሁለት ልጆች እንዳሎት

እና ከባሏ ተፋታ ወደ ቤት ተመልሳ አብራቸው እንደምትኖር ነበር የነገራት….. እንግዲህ

እህቴ ነች ያላት የገዛ ሚስቱን ነበር…..እንደዛ ነው ያሳመናት….ይሄንን መረጃ ሰብስበው

ከሰጡኝ ቡኃላ ..ደወልኩለት

‹‹አቤት ማን ልበል…?››

‹‹አታውቀኝም››

‹‹እሺ ምን ፈለግሽ…?››

‹‹መጀመሪያ የፈለኩትን ከመናገሬ በፊት ስለአንተ የማውቀውን ልንገርህ…ከእናትህ እና

ከሚስትህ ጋር በኪራይ ቤት ውስጥ ትኖራለህ…ሁለት ልጆች አሉህ…ግን የምትተዳደረው

በንግድ ነው..መርካቶ አካባቢ ነው የምትሰራው…አብነት አካባቢ ውሽማ አለህ …ስሟ

መሀሌት ስዩም ይባላል..እንደምታገባት እና የምትኖረውም ከእናት እና ከእህትህ ጋር

እንደሆነ በመናገር ዋሽተሀታል››

‹‹ይሄንን የማይረባ የውሸት ወሬ ከየት ነው የመጣሽው……?››

‹‹ለረጂም ጊዜ ስከታተልህ ነበር …ኢሜል አድርሻህን ሁሉ አውቃለው..አሁን የምነገርህን

መረጃዎች ሁሉ..የአብነቷን ውሽማህ ስለአንተ የነገረችኝን ሁሉ የተቀዳበትን እና

የተቀረፀውን አንድ ላይ አድርጌ ልኬልሀለው..እየው ››

‹‹ከእኔ ምንድነው የምትፈልጊው …?…አስር ሺ ብር..ሃያ ሺ ብር››

‹‹አይ ..ይቺን ይህል ብር እማ… ››

‹‹ሴትዬ እንደዛ ከሆነ ጊዜሽን የተሳሳተ ሰው ላይ ነው ያባከንሺው..የመርካቶ ነጋዴ ነው

ሲሉሽ ከመራካቶ ሀብታሞች ውስጥ አንዱ መስዬሽ ከሆነ ተሳስተሸል…ገና በሁለት እግሬ

መቆም ያልቻልኩ ለፍቶ አዳሪ ነኝ››

‹‹እና ሚስጥሩን ለውሽማህም ለሚስትህም ላከፋፍላቸው…?››

‹‹አይ እንደዛማ አታደርጊም ..ብቻ አቅሜን እየነገርኩሽ ነው››

‹‹እኔ የምፈልገው አሁን ከምትኖርበት ከሮማን ቤት በአራት ቀን ውስጥ ለቀህ እንድትወጣ

ነው…›

‹‹በቃ…?››

‹‹አዎ በቃ…››

‹‹ግን እኮ ገና ያልኖርኩበት ቅድሚያ የተከፈለ የ 3 ወር የቤት ኪራይ አለኝ…እሷ ደግሞ

በፍቃዴ ከወጣው አትመልስልኝም..እንደዛ አይነት አዘኔታ ያላት ሰው አይደለችም..››

‹‹እኔ ካንተ ምንም ጉዳይ የለኝም..ጉዳዬ ከሌላ ሰው ጋር ነው… እንድትጎዳ አልፈልግም..

ዛሬውኑ ቤትህ ፊት ለፊት የሚገኘው ደበበ ኪዬክስ በፖስታ 27 ሺ ብር

አስቀምጥልሀለው..ይሄ ለምታጣው የሶስት ወር ኪራይ ማካካሻ ነው››

‹‹በወር ዘጠኝ ሺ ብር እንደተከራየው በምን አወቅሽ..…?››

‹‹ስለአንተ ብዙ ብዙ ነገር አውቃለው አልኩህ እኮ..እንግዲህ ሶስት ቀን ሰጥቼሀለው..አሁኑ

የኪራይ ቤት መፈለግ ጀምር..ለቤተሰቦችህም ሆነ ለእሷ ምትነግረው አሳማኝ ምክንያት

ይኑርህ..ደግሞ ምንም ይሁን ምንም ስለዚህ ስምምነታችን አንድ ነገር ለማንም

ለሚስትህም ቢሆን ትንፍሽ ብትል በልጆችህ ህይወት መፍረድህን እመን››አልኩ ና ስልኩን

ዘጋውት… ፡፡ስቅጥጥ ነበር ያለኝ…አንድን ወላጅ በልጆቹ ህይወት ከማስፈራራት በላይ ጭካኔ

የለም..ግን አስተማማኝ የሚሆነው ደግሞ እንዲህ ሲሆን ነው… ምርጫ አልነበረኝም፡፡

በዚህ ሁኔታ።።።ድርድር ነው ሰውዬው በተሰጠው ቀን ቤቱን ለቆ የወጣው…ቤቱ በተለቀቀ ማግስት ነበር ደላሎች ሌላ ሰው ለማስጋባት መራወጥ የጀመሩት..ግን ለዝግባውና

ለስንዝሮ የተሰጣቸው ተልዕኮ ስለነበረ ሁሉም ድርድር አልተሳካም..ዋናው አላማችን ቤቱን

ለዛሬ ተልዕኮችን ባዶ ማድረግ ነው..ሰው እልባ ማድረግ፡፡

የባዶውን ቤት የተቆለፈ በር ለመክፈት ብዙም አልተቸገርን …የበራፍ ቁልፎችን ሰርስሮ

ለመክፈት ያለኝን ችሎታ ከዚህ በፊት የነገርኮችሁ መሰለኝ…ሁለታችን ወደ ውስጥ ገባን እኔ

እና ስንዝሮ…፡፡ኩክሻ እና ዝግባው ፈንጠር ፈንጠር ብለው ድምጽ አልባ መሳሪያቸውን

በተጠንቀቅ ወድረው ጨለማ ውስጥ በማድፈጥ ውጭ ቀርተዋል…

ዕቅዳችንን እቤት ውስጥ ሳንገባ ከውጭ ማድረግ እንችላላን…. ግን አስተማማኝ ለማድረግ

ወደ ውስጥ መግባት አለብን..ስንዝሮ በግራ እና ቀኝ እጆቹ ባለ አስር ሊትር ጄሪካኖችን ይዞ

ነው የገባው..እኔ ደግሞ በለበስኩት ጥቁር ካፖርት ሰፊ ኪስ ውስጥ ከአራት ተቀጣጣይ

የእጅ ቦንቦችን ይዤለው…ስንዝሮ እንደገባን አንደኛውን ጄሬካን አስቀመጠና አንደኛውን ከፍቶ

የጣውላ ንጣፍ የሆነውን የቤቱን ወለል ያዳርሰው ጀመር …ከአሮጌ ጠሬጳዛዎች በስተቀር

ብዙም ዕቃ የሌለውን ቤት በቤንዚል እጥለቀለቀው..ወደ ሌሎች ክፍሎች ሌለኛውን ጄሪካን

ይዞ ጋባ …በሰባት ደቂቃ ውስጥ ስራውን ጨረሰ…

አሁን የእኔ ተራ ነው..አራቱንም ቦንቦች ከኪሴ ውስጥ አወጣው…እነዚህን ቦንቦች የያዝኩት

ጠላት ልደመስስበት አይደለም…ጠላት ለመደምስ እማ ወደ እዚህ ባዶ ቤት ሳይሆን ወደ

ጎሮ ነበር መሄድ ያለብኝ ወደ ሰርቢሱ ቤት ..ሮማን ወደምትገኝበት ክፍል…ግን አሁን ጊዜው

አይደለም…

አሁን ቦንቦቹ ያስፈለጉኝ ይሄንን ቤት ድርምስምሱን እንዲያወጡልኝ ነው..ከብሎኬት የተሰራ

ሲሚንቶ ቤት ስለለሆነ እሳትን መቋቋም አቅሙ ጥሩ ሚባል ነው…የቤቱ ግድግዳ ጠቋቁሮ

ኮርኒሱ ብቻ ተቃጥሎ ሊተርፍላት ይችላል..እንደዛ እንዲሆን ደግሞ ፍጽም አልፈልግም…

ይሄ ቦንብ ግን ከእሳቱ ጋር ሲዋሀድ ሚፈጥረው ፍንዳታ ሁሉን ነገር ወደ ፍርስራሽነት

ይቀይረዋል….ከዛ ያቺ እባብ ይሄ ሲሆን ቆማ ታያለች…በውስጥ ልብሷ በድንጋጤ ተነስታ

እንደእብድ ጊቢውን እየዞረች ከሚቃጠለው ቤቷ የሚንበለበለው የእሳት ወላፈን ፊቷን

እየገረፋት ውስጧን እያነፈራት…የመጀመሪያ ቅጣቷን ትቀበላለች…ከዛ ሌላ አራት ተከታታይ

ቅጣት ይቀራታል…መጨረሻው ነፍሶን መንጠቅ ነው፡፡

አራቱን ተቀጣጣይ ቦንቦች ጥሩ ነው ያልኩበት ቦታዎች አስቀመጥኩና ጨረስኩ ..ከስንዝሮ

ጋር በምልክት ተነጋገርንና በየአንንዱ ክፈል አንድ የክብሪት እንጨት ለኩሶ ወደ ወለሉ

በመጣል ከቤት ወጠጣን.…የእሳት ነበልባል በቤቱ ዙሪያ መሽከርከር ጀመረ..እቤቱን

ዘጋውና መንገዴን ቀጠልኩ…

ስንዝሮ ከኃላ ተለከለትሎኛል..ግቢውን ለቀን ወጣን …ኩኩሸና ዝግባውም ተከተሉን…

አስተማማኝ እና ሰዋራ ቦታ እስክናገኝ እርምጃችንን አልገታንም…የሚንበለበል የእሳት

ላንቃ.. የሚትጎለጎል ጭስ መታየት ጀመረ…ምንም አይነት እንቅስቃሴ ሆነ የሰው ድምፅ ግን

አይሰማም…የእሳቱ ኃይል እየጨመረ..ከዛ እኔን እራሴን የሥደነገጠኝ ፍንዳታ ተሰማ…በአንድ

ደቂቃ ልዩነት ሌላ ተመሳሳይ ፍንዳታ ..ከዛ ኹኹታ….የሰፈር ቤቶች ሁሉ መከፈትና

መተረማመስ…ከዛ በላይ እዛ መቆት እራስን ለአደጋ ማጋለጥ ስለሆነ መንገዴን ቀጠልኩ….

ከሲኦል የተለቀቀ የሚመስለውን የሮማንን የጮኸት እና የድረሱልኝ ድምጽ ልክ እንደሙዚቃ

እያዳመጥኩ ጓደኞቼን ይዤ ወደ ቤት….የመጀመሪያ ተልዕኮ እንዲህ ተፈ ፀመ..ውጤቱን

ነገ ሲነጋ በብርሀኑ የምናየው ይሆናል..ስድሥት ሠአት ነው ከእንቅልፌ የተነሣሁት...ፈልጌ ወይንም እንቅልፌን ጨርሼ አይደለም...ጋሼ ዜና ናቸው የቀሰቀሱኝ...በንዴትና በቁጣ ነበር በራፉን በከዘራቸው እየቆረቆሩ ሲራገሙ ....

<<...ማነው...ምን ተፈጠረ....?>>ከአሥፈሪ ቅዠቴ ተላቅቄ በድንጋጤ ድምጽ አውጥቼ ጠየቅኩ..

<<አንቺ መናጢ...ክፈቺ>>

<<እርሶ ኖት እንዴ....?>>የተጨናበሰ አይኔን እያሻሸሁ እንደምንም አልጋዬን ለቀኩና በሩን ከፈትኩ..ገፍትረውኝ ወደ ውሥጥ ገቡና በቤት ውሥጥ በሚገኘው አንድ ብቸኛ ወንበር ላይ ተቀመጡ...ጥያቸው ወደ ሽንት ቤት አመራሁ...ሽንቴ ሥለመጣብኝ ብቻ ሳይሆን ስለደነገጥኩና ሥለፈራዋቸውም ጭምር ነበር...ተፀዳድቼ እና ተረጋግቼ ሥመለሥ ከቅድሙ በመጠኑ ነቃ ብዬ ነበር...

በራፉ ሲንኳኳ ፓሊሥ ነበር ..ያው ፈሥ ያለበት ዝላይ አይችልም ይባል የለ...ለነገሩ ጋሼም ከፓሊስ ብዙም አይሻሉም..የእሳቸው ስድብና ቁጣን መቋቋም እራሡ ለእኔ ከባድና አሥጨናቂ ነገር ነው።

<<ጨረሽ...?>>

<<አዎ ምነው ሠላም አይደሉም እንዴ...?>>

<<እረ ባክሽ ትቀላምጂብናለሽ አይደል...?>>

<<እንዴ ጋሼ!!!>>

<<ዝም በይኮ ነው የምልሽ>>ከዘራቸውን እያወዛወዙ እና ሊቀነድቡኝም እየቃጣቸው...

<<እሺ  ዝም አልኩ...ግን ምን አጠፋሁ..?>>

<<ለሊት የት አባሽ ነበርሽ...?>>

<<እቤቴ>>

<<እቤትሽ....ምን አይነት ደረቅ ነሽ ልጄ...ለመሆኑ ብቻሽን ነው እንደዛ ያደረግሽው..?>>

<<ምኑን ...?>> ጋሼ ምን ለማለት እንደፈለጉ ገብቶኛል...ሥለማታ ተልዕኳችን ሰምተው ነው እንዲህ እሳት ለብሰው እሳት ጎርሰው የመጡት....

<<ሥንት አመት መክሬሽ...ሥንት አመት ለምኜሽ...እርሻት....ከአእምሮሽ አውጪያት...ኑሮሽን ኑሪ ብዬሽ...ሥንት ነገር ተነጋግረን ..የእሷን ቤት አወድማለሁ ሥትይ አንቺ እራሥሽ ወድመሽ ቢሆንሥ ኖሮ...?እረ ምኗ ጉድ ነሽ...ለመሆኑ እንዴት እንዴት አድርገሽ ነው ያን የሚያህል ህንጻ ወደ አመድና ፍርሥራሽነት የቀየርሽው.....?>>

በተዘዋዋሪ ብሥራት ነገሩኝ...ይሄንን ሥሠማ በጣም ደሥ አለኝ...አዎ ይሄንን የምሥራች ለመሥማት ሥንት አመት ጠብቂያለሁ...ሥንት ለሊት እንቅልፍ አጥቼ ሳሰላሥል አድሬያለሁ....

ከዚህ በላይ አይነ ደረቅ መሆን ጋሼን ይበልጥ ማበሳጨት ነው<<ለመሆኑ ያቺ ከይሲ ምን ሆነች...?>>ብዬ ጠየቅኩ....

<<ውይ ሰው እንደዛ አመድ ይነፋበታል...በአንዶኮ ከሠውነት ወደ ጣረ ሞትነት ነው የተለወጠችው...በድን በያት...በቃ በድን....አትናገር አትጋገር..ለፓሊሶች እንኳን ቃሏን መሥጠት አልቻለችም>>

<<እንዴ የምጠረጥረው ሠው አለ አላለችም...?>>

<<እረ እሷ...እንዴት ብላ...በምን አፏ...ብታያት እኮ ኩምሽሽ ብላ አእምሮዋን ያጣች የአማኑኤል ታካሚ ነው የምትመሥለው>>

<<እኔስ ያዙኝ ልቀቁኝ ብላ አገር ትደበላልቃለች ብዬ ነበር...ወደ እኔም ትጠቁማለች ብዬ ተዘጋጅቼ እየጠበኩ ነበር...>>

<<እሱ እንኳን ያው አንቺ እንዳደረግሺው አውቃለች...ለፓሊሥ ግን አልተናገረችም>>

<<እንዳወቀች እርሶ በምን አወቁ...?>>

<<እንደሠማሁ ሂጄ ነበር...አናግሬያታለሁ>>

<<እርሶ እርሷን አናገሯት...?>>

<<አዎ...ምን ለማድረግ እንዳሠበች ማወቅ ነበረብኝ..ጣቷን ወደ አንቺ ለመጠቆም ካሠበች ማሥቆም ነበረብኝ>>

<<ብዙውን ጊዜ ከእሷ ጋር ከማወራ ከሳጥናኤል ጋር ባወራ ይሻለኛል ይሉ ሥለነበር ነው>>

<<ታዲያ በጭንቅ ቀን እኮ ሳጥናኤልንም ቢሆን ማናገር ይናፍቅሻል..>>

<<እሺ ለመሆኑ ምን አለቾት...?>>

<<ሄድኩና የወደመውን ቤት ካየሁ በሁዋላ ወደ አለችበት ሰርቢሥ ገባሁ....ብዙ ሰዎች ነበሩ..ሊያጽኗኗትም ወሬ ለማጣራትም የመጡ...እኔም የማጽናናትና የምመክራት መሥዬ ግን ከሠው ገንጥዬ ወሠድኳትና.....

....ይሄ አሁን የሆነው ከሚገባሽ በጣም ኢምንቱ ነው..በቤት ውሥጥ እያለሽም ከውጭ ቀርቅረን ልናቃጥልሽ እንችል ነበር...ግን ያንቺን ያህል ጨካኝ ሰው ሥላይደለን እንደዛ አላደረግንም...እንድትማሪ እንጂ እንድትጠፊ አንፈልግም...እና አርፈሽ ተቀመጪ...ቢያንሥ በህይወት አለሽ....እፍጨረጨራለሁ ብትይ...ጣትሽን ወደ ሠው እጠቁማለሁ ብትይ....በቀጣይነት ቤትሽን ሳይሆን አንቺን እራሥሽን ነው የምናቃ ጥለው...የሚንቀለቀል እሣት ውሥጥ ነው እንደ ማገዶ የምንከትሽ...የልብ ንጽህና ኖሮሽ እንኳን እንደ ሠለሥቱ ደቂቅ ከእሣቱ የመትረፍ ተሥፋ የለሽም...የገዛ ሀጥያትሽ እራሡ ጋዝ ሆኖ በእሣት ላይ እሣት ሆኖ ነው የሚበላሽ....>>አልኳት....እየተንቀጠቀጠች አዳመጠችኝ...ያቺ ኩሩ ያቺ ጅንን ሴት እንደዛ አንገቷን ደፍታ ሳያት ትንፍሽ እንደማትል ገባኝ...ከእሷ ጋር እንደወጣሁ ነው ወደ አንቺ የመጣሁት...

በደሥታ ከተቀመጥኩበት አልጋ ተሥፈንጥሬ ተነሣሁና የጋሼን ግራና ቀኝ ጎንጮቻቸውን አገላብጬ ሞጨሞጭኳቸው>>

<<ምንድነው እሱ....?የምን ደሥታ ነው....?>>

<<ያሠብኩት ስለተሣካልኝ...እሷን ማሸማቀቅ ሥለቻልኩ...ግን ጋሼ ቆይ እንዲያ ሲያሥፈራሯት ቤቱን በማቃጠሉ እርሶ እንዳሉበት ሲነግሯት የእውነት አምና ትጠቁምዎት ይሆን እንዴ....?>>ሥጋት ቀሥፎ ያዘኝ

<<ታዲያ ምን ሆነና ፍልጎቴ....?አየሽ ካንቺ ሌላ የምትጠረጥረው ሠው ልሠጣት ሥለፈለኩ ነው...ደፍራ ወደ ህግ ከሄደች አንችን አሣልፈ ለመሥጠት እድል ማግኘት የለባትም>>

<<እና....?>>በገረሜታ 

<<እናማ...እኔን አሁን ቀሪ ህይወቴን ቂሊንጦ ገብቼ መንግሥት ቢጦረኝ ምን ይመሥልሻል...?>>

<<አይ ጋሼ......!!!በዚህ እድሜዎ ቅሊንጦ....?ያሾፋሉ>>

<<ምን ይቀርብኛል...?በይ ተነሽ አሁን እንሂድ>>

<<ወዴት...?>>

<<የደሥ ደሥ ምሳ ልጋብዝሻ...ለጀግንነትሽ>>

ፈገግ አልኩ<<...አሁንኮ በሀይለኛው እየተቆጡኝ ነበር>>

<<መቆጣትማ አሁንም እቆጣሻለሁ...ቢያንሥ እንደዚህ አይነት ከባድ ነገር ሥታደርጊ ልታማክሪኝ ይገባ ነበር...ሌላው ይቅር በጉልበት ባላግዝሽ በሃሣብ ማገዝ ያቅተኛል...? ተማክረው የፈሡት ፈሥ አይገማም ይባላል...ያን ባለማድረግሽ አብሽቀሽኛል...ግን ደግሞ የሆነውን ሣይ .....ያቺ መናጢ እንደዛ ኩምሽሽ ብላ ሳይ...በልጄ ጀግንነት አንጀቴ ቅቤ ጠጥቷል...አዎ እንደኮራሁብሽማ ልደብቅሽ አልፈልግን>><<እና የእውነት ይጋብዙኛል?>>

<<በትክክል...በይ ቶሎ ለባብሺና ውጪ>>ብለው ከወንበራቸው በመነሳት ቤቱን ለቀው ወጡ....

ቢጃማዬን አወለቅኩና የሚለበሥ ልብሥ ፍለጋ ሻንጣዬን ከፈትኩ....ሳልፈልግ አይኔ ዋቅቶላ የገዛልኝ ቀሚሥ ላይ አረፈ...

<<ዛሬማ በዚህ በተለየ ቀን የተለየ ነገር ነው የምለብሠው>>አልኩና አውጥቼ ለበሥኩት...ቀሚሱን ስለብስ እሱን እራሱን የለበሥኩት ነው የመሰለኝ...አጠገቤ እንዳለ ወይም እንዳቀፈኝና በሠውነቴ እንደተጠመጠመብኝ አይነት ሥሜት ተሠማኝ...ለብ ያለ የሙቀት ስሜት ...ጫማዬን አጥልቄ ቤቱን ቆለፍኩና ወጣሁ...ጋሼ በዝግታ እየተራመዱ ሲጠብቁኝ ደረሥኩባቸው...

<<አይ የእኔ ልጅ...ቆንጅዬኮ ነሽ>>

<<ቀሚሥ ሥለብሥ ግን በጣም አፍራለሁ>>አልኳቸው...የእውነት ራቁቴን ጎዳና ላይ የምሄድ ነው የሚመሥለኝ

<<አይ ጊዜ....>>አሉ እንደልማዳቸው<<አይ ጊዜ ድሮ በእኛ ጊዜ አንድ ሴት ሱሪ ስትለብስ ነበር...በእፍረት አቀርቅራ የምትሄደውና እርምጃ ሁሉ ጠፍቶባት እግሯ ሚምታታባት...ዛሬ ይሄው ባንቺ ጊዜ ቀሚስ ስትለብሺ ታፍሪና እርምጃ ሲጠፋብሽ ሳይ ከመገረም ውጭ ምን አደርጋለሁ...>>

ጋሼ ምግብ ከጋበዘኝ በሁዋላ ተለይቼያቸው ልሄድ ፈልጌ ነበር...ግን<<ዛሬማ ውልፍች የለም....አብረን ውለን አብረን ነው የምናድረው>>አሉኝ።

<<እንዴ ጋሼ ከጓደኞቼ ጋር ቀጠሮ አለብኝ>>

<<ምን ልትዶልቱ....?ተናግሬያለሁ ንቅንቅ የለም>>ቆፍጠን ብለው አሥጠነቀቁኝ....ጨነቀኝ የእውነቴን ነቅ ዛሬ ከሥንዝሮ ጋር ቀጠሮ ነበረብኝ..ሥለነገ የሁለተኛ ዙር ጥቃታችን ዝርዝር ዕቅዶችን የምናወጣው ዛሬ ነው...ግን ደግሞ አሻፈረኝ ብዬ ጋሼን ተራምጄ መሄድ አልችልም...ተያይዘን ወደ ቤት ሄድን..

ቤቱ ባዶ ነበር..ከፍተን ገባን...ጋሼ አልጋቸው ላይ አረፍ ሲሉ..እኔ ደግሞ ቡና ላፈላ ሽር ጉድ ማለት ጀመርኩ<<ልጄ ቡና ልታፈይልኝ እንዳይሆን>>ጠየቁኝ የህጻን ጉጉት በሚመሥል ሥሜት

<<መጠርጠሩሥ>>

<<አቤት ቡናሽንኮ እንደምናፍቅ...አንቺን እራሥሽን አልናፍቅሽም...>>

<<እሱ እንኳን ውሸት ነው..ከኔ ሚበልጥቦት የለም>> በኩራትና በጉራ መለሥኩላቸው....ነገሩ ጉራ ማለት እንኳን ይከብዳል....አዎ በጣም እንደሚወዱኝ...አንድ አባት ልጁን ከሚወደው እኩል እንዳንዴም ከዚያ በላይ እንደሚወዱኝ ነው ሁሌ ውሥጤ የሚነግረኝ...ውሥጤን ደግሞ አምነዋለሁ...

<<እሱንስ አልሳትሽም...ካንቺ ውጪ ማን አለኝ ብለሽ ነው>>አሉኝ ትክዝ በማለት..

ወደ ቡና ማፍላቴ ከመሄዴ በፊት ሥልክ ደውዬ ለጓደኞቼ ቀጠሯችን መሰረዙን መናገር አለብኝ...ስልኬን አነሳሁና ከፈትኩት....ለሊት ከተልእኮዬ በተመለስኩበት ወቅት እንደዘጋሁት ነበር...ላለመረበሽ...

ደወልኩና ለስንዝሮ ነገርኩት..ዘግቼ ላሥቀምጠው ስል...ጢጥ...ጢጥ የሚል ድምጽ ማሰማት ጀመረ...ሚሴጅ ላክ 35 የሚል ቁጥር አየሁ<<እንዴ ምን ጉድ ነው....?>> 35 ሚሴጅ ...ከፈትኩት..ሁሉንም ተርትሬ አየሁት ከሁለት ቴሌ ከላካቸቅ የዘወትር አሠልቺ ማሥታወቂያ መልእክቶች በስተቀር ሌሎቹ ከዋቅቶላ የተላኩ ናቸው...በዛሬው ግማሽ ቀን ውሥጥ ተላኩ

<<ሰላም አለሽልኝ የእኔ ፍቅር>>

<<ስልክሽ ምነው ተዘጋ?>>

<<ስራሽን አልተውሺውም ወይ?>>

<<ይህ መልእክት እንደደረሠሽ ደውይልኝ>>

<<ይሄን ሁሉ ሰአት እንዴት ሠው ሥልኩን ይዘጋል....?ሰው ያሥባል ብለሽ አታሥቢም እንዴ...?እንዴት አይነት ድንዙዝ መሆን ነው?>>

<<ምን አይነት ደንዳና ልብ ነው ያለሽ?>>

<<በጣም ታሥጠያለሽ...የማትረቢ ነሽ>>

<<በጣምኮ ነው የምወድሽ...ማበዴ ነው>>

.

.

.

.......ሁሉንም አንብቤ መጨረሥ አልቻልኩም..ገረመኝም...አሳዘነኝም...ደወልኩለት... ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ ናቸው ይላል...ደግሜ ሞከርኩ አይሠራም...

<<ያንተ የራሥህም ስልክ አይሠራም...ደግሞ በአገር ሠላም ምን እንደዚህ ያነጫንጭሃል...?ባል ሆንክብኝኮ>>ብዬ መልእክት ላኩና ቀና ስል ጋሼ ለካ ነገረ ሥራዬን ይከታተል ኖሮ

<<ሰላም ነው ልጄ?>>ሲል ጠየቀኝ

<<አይ ሰላም ነው... ያ ነጭናጫ ሰውዬ ነው>>መለሥኩለት

<<ተይ አንቺ ልጅ...ይሄን ሠውዬ ሳላየው ቀልቤ ወዶታል...ጣል ጣል  አታድርጊው...ሁዋላ በተወደደ ባል እንድልታጪውና እንዳይቆጭሽ>>

ንግግራቸው ፈገግ አሥባለኝ<<ተወዷል እንዴ...?እኔኮ ባል አምሮኝ ልገዛ ወጥቼ ሥለማላውቅ ዋጋውን አላውቅም....ስንት ገባ...?>>በማለት ቀለድኩና ስልኬን ከጋሼ ጎን ጠረጴዛ ላይ ወርውሬ ቡና ልገዛ ወደ ኪዬክስ ወጣሁ....

.

.

.ሰንደሉንም... እጣኑንም..ቄጤማውንም...ቡናውንን ገዝቼ በአሥት ደቂቃ ውሥጥ ተመለሥኩ...።ከሠል አቀጣጠልኩ...ሲኒውን አቀራረብኩ...ቡናዬን አጠብኩና ቆላው...ጭስስ ብሎ ጭሱ ተትጎለጎለ ማንከስከሻ ወስጄ ወደ አፍንጫው አሥጠጋሁለት እና ቡናውን እንዲያሸት አደረኩት <<ሰማያዊ ሽታ በህይወትሽ ይሙላ>>ብለው መረቁኝ...

ቡናውን ወቀጥኩና አፈላዋ....ጋሼን አጠጣሁዋቸው...እኔም ጠጣሁ...ከተመ...ተመረቅኩ በጣም ተመረቅኩ...ከዛ እቃውን አጣጥቤ ካነሳሳሁ በሁዋላ...ከጋሼ ጎን ጋደም አልኩ...

እሳቸው እያወሩልኝ እኔ እያዳመጥኩ ብዙ ብዙ ከተጫወትን በሁዋላ በመሃል ስልኬ ጮኸ ተንጠራርቼ አየሁት...ዋው ዋቅቶላ ነው...ደሥ አለ ኝ ደውሎ ሊነጫነጭብኝ እንደሆነ ባውቅም መደወሉ ደሥ አሠኝቶኛል.....

ከዛም አልፎ ሊሠድበኝ ሁሉ እንደሚችል ብገምትም ማንሣቴን አላቆምኩም....በቃ የሆነ የበረሀ ጉዞ ላይ አንድ ጉንጭ የፊሪጅ ውሃ ገረገጭ ሲያደርጉ የሚሰማ አይነት የእርካታ ሥሜት ነው በመደወሉ ምክንያት የተሠማኝ...ተሥተካክዬ ቁጭ አልኩና አነሣሁት

<<ሄሎ>>ክው አልኩ...ድምጹ የዋቅቶላ አይደለም...እረ እንደውም የወንድ ድምጽ አይደለም..ማን ነች በእሱ ሥልክ የደወለችልኝ....?ውሽማ ትሆን እንዴ.....?ይሄን ሳስብ ልቤ ላይ ጦር የተሠነቀረብኝ መሰለኝ...<<ከዋቅቶላ ሥር ራቂ...ከእሱ ጋር እየተደዋወልሽ አትረብሽኝ>> ልትለኝና ልትሠድበኝ ነው አይደል የደወለችው...?ደም ሥሬ ሁሉ ግትርትር አለ...ልክ ሮማን ፊት ለፊት ለጠብ እንደቆምኩ አይነት....

<<ምን ነበር....?>>ደዋዬ የምታየኝ ይመሥል ኮሥተርተር ብዬ

<<ይቅርታ...ከሻንቡ ሆስፒታል ነው የምደውለው...>>

<<ምን?..ሆስፒታል...ሻንቡ>>አፌን የሞላው ምራቅ ወደ እሬትነት ተቀየረ

<<ተረጋጊ እህቴ...ከዚህ ሥልክ ላይ ያየሁት የመጀመሪያው ቁጥር ያንቺ ሥለሆነ ነው...ታውቂዋለሽ...?>>

<<አዎ በጣም አውቀዋለሁ...ምን ሆነ...?>>

<<ባለቤቱ ነሽ?>>

<<አይደለሁም ጓደ ኛው ነኝ....ምን ሆኗል እያልኩሽኮ ነው?>>አንባረቅኩባት

<<አይ ድንገተኛ ህመም ነው...እራሡን ሥቶ መንገድ ላይ ወድቆ ያገኙት ሠዎች አምጥተውት ነው...ያመጡት ሠዎችም ማንነቱን አያውቁቱም..>>

<<ምን ማለት ነው...?እንዴት ነው አሁን?>>የምለው የምናገረው ጠፋኝ<<እራሱን እንደሳተ ነው...ግን ለክፉ የሚሠጠው አይመሥለኝም..ምርመራ ላይ ነው...መምጣት ብትችይ>>

<<ከየት ነው የምመጣው?>>

ደዋዬ ተደነባበረች<<እንዴ ሻንቡ አይደለሽም እንዴ?>>

<<አዲስ አበባ ነኝ>>

<<ኦ ይቅርታ...በቅርብ ያለ ዘመድ ወይም የጓደኞቹን ሥልክ ትሠጪኛለሽ....?

<<አላውቅም...>>

<<እሺ ችግር የለውም በሥልኩ ላይ ሌላ ቁጥር ፈልጌ ቤተሠቦቹን ለማግኘት እሞክራለሁ>>

ስልኩ ተዘጋ....በድን ሆንኩ...እጄ ሁሉ እየተንቀጠቀጠ ነው<<ምን ሆንሽ ልጄ....?..ምን ሰማሽ...?>>

<<ታ..ሟ..ል>>ቅርፍፍ ባለና በደከመ ድምጽ መለሥኩላቸው ለጋሼ

<<ምን ነካው ልጄ...?ዋቅቶላ ሥትይ ሰማሁ ልበል?>>

<<አዎ...>>

<<አይዞሽ መታመም ያለ ነው ...አትደንግጪ>>ግንባሬን እያሻሹልኝ

<<ሆስፒታል ገብቷልኮ ነው የምትለኝ?>>

<<አይዞሽ...ምንም አይለው..ሁኔታውን አይተን ካልተሻለው ነገ ወይም ተነገ ወዲያ ሄደሽ ታይዋለሽ>>

<<ሄደሽ?>>በርግጌ አፈጠጥኩባቸው

<<አዎ...ምን አለበት ጓደኛሽ አይደል>>ተቃውሞ ያሠማሁ መሥሏቸው..

<<አይ ማለቴ አሁኑኑ ነው መሄድ የምፈልገው...ከአልጋው ላይ ተሥፈንጥሬ ተነሣሁ...ጋሼ አሁኑኑ መሄድ አለብኝ>>ቁርጥ ውሳኔዬን አሰማሁ....

<<እረ ተረጋጊ ካልሆነ ጥዋት ትሄጂያለሽ>>

<<እንዴት ሆኜ አድሬ?>>

በዚህ ንግግሬ ጋሼ ፈገግ አሉ...<<ምነው ልጄ ጀግና አይደለሽ እንዴ>>አሉኝ ፈገግ ብለው የእሳቸው ፈገግታ እኔን አበሳጨኝ..ግንባራቸውን ሥሜ ተሠናበትኳቸውና ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ...እያጉረመረምኩ..ጀግና አይደለሽም ወይ ይሉኛል እንዴ?

ጀግንነትን እዚህ ጋር ምን አመጣው...ከሮማን ጋር ለመፋለም ካልሆነ በሥተቀር ከዋቅቶላ ጋር ለመፋቀር ጀግንነት ምን ይፈይድልኛል...?ምን እያወራሁ ነው...?መፋቀርን ምን አመጣው...እኔና ዋቅቶላ ፍቅር...ምን ለማለት ፈልጌ ነው..?ስገርም?።

ብቻ ዋናው ጋሼ ግራ አጋብተውኛል...እንዳልሄድ አልተጫኑኝም..እረ በተሠማኝ ድንጋጤና ሀዘንም ብዙ ትኩረት የሰጡት አልመሰለኝ...ከፋኝ...ቀጥታ ወደ ቤቴ እየሄድኩ እሱባለው ጋር ደወልኩለት...የያዘውን ስራ አቋርጦ ሚኒባሷን እቤት ድረሥ ይዞ እንዲመጣ...ዛሬውኑ መብረር አለብኝ...ሰአቴን ተመለከትኩ...9 ሰዓት ሆኗል..በቃ መንገድም ቢሆን አድራለሁ እንጂ ዛሬውኑ መሄድ አለብኝ...ወሠንኩ.........ጂጂ.....


ከተማዋን ለቀን ወጥተን ቡራዩ ሥንደርሥ ከቀኑ 10 ሰዓት ሆኖ ነበር<<...በቃ እንደዚህ ነው የምትነዳው...>>

<<ማለት...?>>

<<በእግር እየሄድንኮ ነው የሚመሥለው>>

<<ከተማ ውሥጥኮ ነው ያለነው...30 የሆነው በምክንያት ነው ሲባል አልሠማሽም>>

ዝም አልኩት..ምን ብዬ ልከራከረው..እሡ ያለው ትክክል ነው...ህግ በሚፈቅድለት አግባብ የሞያ ሃላፊነቱን አክብሮ እየነዳ ነው ...እኔ ነኝ እንጂ የገዛ ሥሜቴን መሾፈር ያቃታኝ...።

እኔ አሁን በዚህ ሠአት በመኪና ተጭኖ በሚሽከረከር ጎማ ኪሎሜትር እየቆጠሩ መጓዝ አይደለም የምፈልገው...አቋራጩን ይዤ ሠማዩን ሰንጥቄ ክንፍ አውጥቼ መብረር ወይም ክንፍ ባለው ነገር ላይ ተንጠልጥዬ መክነፍ ነው የምፈልገው.. .

አሁኑኑ ሥሩ መገኘት...ግንባሩን ማሻሸት..እጆቹን መዳበሥ..ህመምን ማገዝና እሡን መንከባከብ ነው የምፈልገው...።ዳሩ ምን ያደርጋል ሠው የመሆናችን ዋናው ክፋቱኮ ውሥንነታችን ነው....ማድረግ በምንፈልገው የውሥጥ ፍላጎታችንና ማድረግ በምንችለው አቅማችን/ችሎታችን/መካከል ያለው የትየሌለ ልዩነት ነው...

<<መንፈሥ መሆን ነበር>>አልኩ ሳላሥበው ድምጽ አውጥቼ..

<<እረ በሥመአብ በይ>>አለኝ ሹፌሬ እሱባለው..ከእሱ ጋር መጨቃጨቅ አቆምኩና ሞባይሌን ከቦርሳዬ አወጣሁ...ደወልኩ...

"ሄሎ"

<<ሄሎ ማን ልበል...?>>

<<ቅድም የደወልሽልኝ ልጅ ነኝ..>>

<<እእእ..የአዲሣባዋ...?>>

<<አዎ...በእናትሽ እንዴት ነው...?>>

<<አይ...አሁን ደህና ነው...>>

<<ሊያናግረኝ ይችላል...?>>

<<እረ እንደዛማ አይደለም...ማናገር አይችልም...በዛ ላይ አሁንም ህክምና ላይ ነው...ምን አልባት ነገ ካልሆነም ከነገ ወዲያ ነው ልታናግሪው የምትችይው...>>

<<ዘመዶቹ አልመጡለትም.....?አላገኘሻቸውም...?>>

<<አይ አግኝቼያቸዋለሁ...እህቱ መጥታለች...ታናግሪያታለሽ ላገናኝሽ...?>>

<<አይ አታውቀኝም ይቅርብኝ...ባይሆን ቆይቼ አንቺኑ ደውዬ ሥለ ሁኔታው ብጠይቅሽ ይሻላል...እኔም እየመጣሁ ነው>>

<<በእውነት....?እየመጣሽ ነው...?>>የተደነቀና የተገረመ ድምጽ...ግራ ገባኝ....እመጣለሁ ማለቴ ልጅቷን ለምንድነው እንዲህ ያሥደነቃት....?የእኔ መምጣት ለእሷ ፋይዳው ምንድነው.....?ሥልኩን ከዘጋሁ በሁዋላ ሥለዚህ ጉዳይ ነበር የማሥበው...

ጉደር ሥንደርሥ 12 ሰአት ሆነ..እሡባለው እሱ ከሚፈልገው በጣም ፈጠነ አንዳንዴ እኔ ከምፈልገው ደግሞ በተንቀረፈፈ ሁኔታ እየነዳ ነው...ጭራሽ መንገዱን እያጋመሥን ሥንመጣ እና ሠአቱም ወደ ምሽቱ ሲቃረብ ጭንቀቴ በእጥፍ ጨመረ...መልሼ ሥልኬን መጎርጎር ጀመርኩ...ሥልኩ አይሠራም ...ደግሜ ደወልኩ<<የደወሉለት ደንበኛ ሥልክ ጥሪ አይቀበልም>>አለኝ

<<ምን አይነት ብሽቅ ነኝ...?>>

<<ምን ሆንሽ ደግሞ...?>>አለኝ እሱባለው በአንድ አይኑ የፊት ለፊቱን መንገዱን እያየ በአንድ አይኑ ደግሞ ሸርፎ እኔን እያየኝ እና በትዝብት እየሸረደደኝ....

<<ሥልኩ አይሠራም>>

<<የማን....?>>

<<የዋቅቶላ ነዋ...በእሡ ሥልክ ነበር ነርሷ ሥታናግረኝ የነበረው...አሁን ጥሪ አይቀበልም ይላል>>

<<ባትሪ ጨርሶ ይሆናላ>>

<<እ ሱማ እንደዛ ሆኖ ነው..ግን የነር ሷን ሥልክ መቀበል ነበረብኝ>>

<<ይዘጋል ብለሽ ስላላሰብሽ ነዋ>>ሊያጽናናኝ ሞከረ

<<እኮ ማሠብ ነበረብኝ...እሺ አሁን ምን ይውጠኛል...?>¢

<<ምን ይውጠ ኛል....?መታገሥ ነዋ....ወደዛው እየሄድንኮ ነው>>

<<እኮ....እዛ እሥክንደርሥሥ....>>

<<እረ  ሲሱ ተረጋጊ....ከመቼ ጀምሮ ነው ፎንቃ እንዲህ የጠለፈሽ...በእውነት በጣም ነው የገረመኝ>>

<<ምኑ ነው የሚገርምህ...ምን ወሬ ታበዛለህ..አሁን በህይወትና በሞት መካከል ሥላለ ሠው ማሠብና መጨነቅ በፎንቃ ከመያዝ ጋር ምን አገናኘው...>>

<<እረ ቀዝቀዝ...እንዲሁ ለጨዋታ ነው ያነሣሁት>>

<<ቢሆንሥ....?ዝም ብለህ ትዘባርቃለህ እንዴ....?>>

<<ይቅርታ አልኩ እኮ>>ግራ ገብቶትና ደንግጦ.....

<<በል እሺ አፍጥነው>>

<<ይቅርታ...እሡን አልችልም>>

<<ማለት...?>>አልኩት...ደም ሥሬ ሁሉ ግትርትር ብሎ በጥርሤ ልዘነጥለው በጥፍሬ ልቦጫጭረው እየዳዳኝ።...

<<ማለትማ ዳገትና ገደሉን እያየሽው አይደል እንዴ.....?በሠላም የፈለግሽው ቦታ ደርሠሽ ማየት የምትፈልጊውን ሠው ለማየት አትፈልጊም..?

<<እሡማ እፈልጋለሁ...>>አልኩ ቀዝቀዝ ብዬ...የመንገዱን ግራና ቀኝ እያየሁ...

...እውነቱን ነው አሁን ወደሚታየኝ ገደል መኪናዋ ተሽቀንጥራ ሥትገለባበጥና ሁለመናችን ብትንትን ሲል በአይነ ህሊናዬ ታየኝና ዘገነነኝ።ከዛም አልፎ ውሥጤ ሽብር ተሠራጨ...ሞትን በዚህ መጠን ሥፈራ የመጀመሪያ ልምዴ ነው....

በቀደመ ልምዴ ብሞት ምን አጣለሁ....?ከህይወትሥ ምን አገኛለሁ....? ብዬ ለመጠየቅ በምገደድበት አጋጣሚ ከውሥጤ አገኝ የነበረው መልሥ...በመሞት እና በመኖር መካከል ያለውን ልዩነት ምንም ነው የሚል ነበር።....አሁን ግን ለመኖር ያለኝ ጉጉት ሣላውቀው ወደ ላይ ተሥፈንጥሮ ሠማይ ላይ ተሠቅሎ አገኘሁት...ይሄን የታዘብኩት ደግሞ አሁን ነው..አሁን በዚህቺው ደቂቃ..

በሥንት ጣርና መከራ ከምሽቱ 2 ሰአት አካባቢ ፊንጫ ከተማ ደረሥን።ግራ ገባኝ...እንቀጥል ወይሥ አልጋ ይዘን እዚሁ ፊንጫ አድረን ለሊት እንሂድ.......?

<<ምን ትላለህ......?>>አልኩት በራሴ መወሠን አቅቶኝ

<<ምኑን በተመለከተ...?>>

<<እንቀጥል ወይሥ እዚሁ ፊንጫ አድረን ለሊት እንሂድ....?>>

<<እንደኔ እንደኔ እዚሁ ብናድርና ለሊት ብንበር ይሻላል ባይ ነኝ...አሁን ብንሄድም እዛ ሥንድርሥ አራት ሠአት ያልፋል...በዛ ሠአት ደግሞ ሆሥፒታልም መግባትና ማየት አንችልም...አልጋም ልናጣ እንችላለን>>

<<አልጋው እንኳን ችግር የለውም ላንድ ቀን መኪና ውሥጥ ብንተኛሥ ለአንድ ቀን ምን አለበት....?>>አልኩት በትዝብት።

<<አይ እንደፈለግሽ....ንዳ ካልሽኝ ልንዳው>>አለ ኝ

<<ንዳው ልበለው ወይሥ ምን ይሻላል....?እያልኩ ከራሴ ጋር ሥወዛገብ ሥልኬ ጠራ....አየሁት።ጋሼ ናቸው።>>

አነሣሁት <<ጋሼ ምን ይሻለናል....?በጣም ነው የጨነቀኝ....? ሻንቡ መድረሥ አልቻልንም.....?እሡባለውን ዛሬ ቢያዩት በጣም ለግሟል...መኪና የሚነዳ ሣይሆን ጋሪ የሚገፋ ነው የሚመሥለው....አሁን ፊንጫ ከተማ ነን...ብንሄድም ሆሥፒታል መግባት አንችልም ብሎኛል...ሥልኩም አይሠራም..በጣም ጨንቆኛል>>ተንጣጣሁባቸው።

<<ልጄ አይዞሽ ተረጋጊ....በቃ ጥሩ ተቃርበሻል እኮ....ሥለዚህ አሁን እዛው ያላችሁበት እደሩ...ከዚያም ለሊት ተነሱና በጥዋቱ ትደርሣላችሁ....>>

<<እንደዛ ይሻላል ጋሼ...?>>

<<በእኔ ይሁንብሽ እንደዛ ነው የሚሻለው...በሉ አሁን መኝታ ፈልጉ...እራሥሽን አረጋጊና እራት በልታችሁ ተኙ>>

<<እሺ ጋሼ>>

<<በይ ደህና እደሪልኝ....ጥዋት እንደደረሽ እና የልጁን ሁኔታውን እንዳየሽ ደውይልኝ>>

<<እደውልሎታለሁ ጋሼ...አመሰግናለሁ>>ሥልኩ ተዘጋ....ወደ ያዲ ሆቴል መኪናችንን አሥገባን..ይሄ ሆቴል ከከተማዋ የተሻለውና ትልቁ ነው...ጎን ለጎን ሁለት አልጋ ያዝን..ወደየክፍላችን እየገባን ሣለ አሥቆመኝና<<…ቦርሣሽን አሥቀምጪና እራት እንውጣ...?>>አለኝ እሡባለው

<<አይ አንተ ወጣ በልና ብላ...እኔ ማረፍ ነው የምፈልገው>>

<<እረ ተይ...ለሊት ይርብሻል>>

<<ግድ የለህም..ይቅርብኝ>>

<<እሺ እዚሁ ይምጣልሽ....?>>

<<አይ አልፈልግም...ለሊት 11:30 እቀሠቅሥሃለሁ>>

<<ጥሩ ተሠናብቼው መኝታ ቤቱን ዘጋሁና...አልጋዬ ላይ ዘፍ አልኩ...ልተኛ  ሳይሆን ልተክዝ...

.

.

.

.

ዋቅቶላ...

እሷ መልሳ ካልመጣች በሥተቀር ምንም የምነግራችሁ ነገር የለም ብያችሁ ነበር..አይደል..?አሁን እንግዲህ አንሥቼዋለሁ...።እናንተም ናፍቃችሁኝግ ነበር....እውነቱን ለመናገር ግን ያው በእናንተ ለመወደድ ካልሆነ በሥተቀር እንኳን ልትናፍቁኝ ትዝ ብላችሁኝም አታውቁ...እውነቴን ነው...በዛ ሁሉ ሃሣብ...በዛ ሁሉ እራሥንም እሥከመርሣት በደረሠ መብሠልሠል ውሥጥ እንዴት ሥለእናንተ ላሥብ እችላለሁ.....?እራሴንም ረሥቼ ነው የከረምኩት...እንዴ !!!!!!!ለካ ፍቅር የሚባለው ውጥንቅጥ ሥሜት እንዲህ ነው እንዴ.......?እረ እንዲህሥ ከሆነ ለጠላትም አይስጥ...

አሁን ወደ ዛሬው ጉዳይ ልመለሥላችሁ...በደሥታ ጦሽ ልልላችሁ ነው..ጠረኗ እየሸተተኝ ነው...አዎ እኔ ወዳለሁበት እየቀረበች ነው..ይታወቀኛል...እድሜ ለአንድ ሠው...እድሜ ለጽድቁ ሽማግሌ...ለካ ወዳ አይደለም እሷም እንደዛ የምትወዳቸው እና ሁሌ ከአፏ የማይጠፉት...የሆነው እንዲህ ነው...ዛሬ ሰባት ሰዓት ላይ ነበር ሥልኬ የጠራው ...ጂጂ ነበረች...ደውዬ ካናገርኳት ከ10 ደቂቃ በሁዋላ ነበር መልሶ የተደወለልኝ..ሳነሳው ግን እሳቸው  ነበሩ...

<<ሄሎ>>

<<ሄሎ ዋቅቶላ>>የሚርገበገብ ደካማ ድምጽ

<<አቤት ማን ልበል...?>>አልኩ ግራ ገብቶኝ..

<<ዜና እባላለሁ...የጂጂ አባት ነኝ ማለት እችላለሁ>>

<<አወቅኮት...ማለት እሷ ሥለ እርሶ ነግራኛለች>>

<<ጎሽ..እንግዲያው አንድ ነገር ልንገርህ...ጂጂ ጥሩ ሁኔታ ላይ አይደለችም>>

አቤት የደነገጥኩት አደነጋገጥ...የቅርብ ዘመዴን ሞት የተረዳሁ ነው ያሥመሠልኩት

<<አይ ማለቴ ለጊዜው ደህና ነች..ግን አሳዳጊዋን ሴትዬ ለማጥቃት እንቅሥቃሤ ላይ ነች..በዚሁ ከቀጠለች ደግሞ ወይ የሆነ ወንጀል ሥትሠራ ትያዝና እሥር ቤት ትወረወራለች አልያም አደጋ ደርሶባት ደመ ከልብ ትሆናለች ብዬ በጣም ፈርቼ ነው>>

<<ታዲያ ምን ላድርግ.....?ይንገሩኝ..ልምጣ እንዴ.....?መጥቼ ልጠብቃት...?>> ሁሉን ነገር ጥለህ ብረር ብረር የሚል ሥሜት ወረረኝ...

<<አይ ልጄ እንደዛ አይደለም...ወዳንተ ውሠዳታ...እንደዛ ነው የሚሻለው>>

<<አይ ፋዘር...እሡንማ ሞክርያለሁ..ብዙ ቀን ለምኛታለሁ..ላሣምናት ..አልቻልኩም እንጂ>>

<<ዘዴ ፍጠራ..የሆነ ዘዴ ከፈጠርክ ሥለምታፈቅርህ ትታለልሃለች>>

<<ሥለምታፈቅርህ ነው ያሉት....?እሷኮ ሠው ማፍቀር አትችልበትም>>

<<አይ ልጄ እሱን እንኳን ተወው..የአፏን ሰምተህ ነው አይደል....?የፍቅር ጉዳይ ልብ ላይ ነው የሚጻፈው እንጂ ምላሥ ላይ አይንጠለጠልም...ከአንደበቷ የሚወጣውን ቃል ሳይሆን የልብ ምቷን አድምጥና ሥለአንተ የምታሥበውን ለመረዳት ሞክር ያን ጊዜ እውነቱን ትረዳለህ...

እኔን ከጠየከኝ በቃ በጣም አፍቅርሃለች...ግን ማመን አልፈለገችም...እንዲህ አይነት ሽንፈት ተሸንፋ ሥለማታውቅ ማመን ከብዷት ነው....>>

<<የሚሉት እውነት ቢሆን ደሥ ይለኛል>>

<<ነው ልጄ እመነኝ...እሷን እድሜ ልኳን ነው የማውቃት..ለማንም ወንድ እንዲህ አይነት ሥሜት ሲሰማት እንዲህም ሥትብሰለሰል አይቻት አላውቅም....እና የምትወዳት ከሆነ ውሰዳት..ደግሞ እመነኝ ምን አልባት የተገናኛችሁት ጥሩ ያልሆነ ቦታ ሊሆን ይችላል..ግን ወርቅ የሆ ነች ልጅ ነች...ለወደደችው የምትሞት የራሴ ላለችው ሠው የምትኖር ልጅ ነች....

<<ፋዘር አውቃለሁ...ሶስት ቀን አብሬ ኑሬ ብዙ ነገር ሥለ እሷ አውቄያለሁ...በጣም ነው የምፈልጋት...እኔ ስላለፈው ደንታ የለኝም..የትናንቷን ጂጂን ሳይሆን የዛሬዋን...አሁን ያለችዋን ጂጁን ከነ ክፍተቷ ነው የምፈልጋት>>

<<ተባረክ ልጄ...ጥሩ ሰው ነህ....ወድጄሃለሁ...እና ተሥማምተናል ማለት ነው አይደል...?>>

<<ምኑ ላይ ነው የተሥማማነው ፋዘር...?>>

<<ትወሥዳታለህ..?>>

<<እንዴት አድርጌ ፋዘር...?>>

<>ይሄውልህ እኔ አንድ ዘዴ አለኝ..ከአንድ ሰአት በሁዋላ ደውልላት..>>

<<ደውዬሥ...?>>

<<ማለቴ አንተ ሣትሆን በሌላ ሠው ትልሥደውልልና አንተ አደጋ ደርሣሶብህ እራሥህን ሥተህ ሆሥፒታል እንደገባህ እንዲነግሯት አድርግ>>

<<እንዴ ጋሼ...ይሄ ምን ይጠቅማል....?>>

<<እሷን ወደ አንተ ለማምጣት ነዋ>>

<<እረ አትመጣም>>

<<ሞክርና እየዋ...በል ቻው አሁን እየመጣች ነው>>ብለው ሥልኩን ዘጉብኝ...10 ደቂቃ እዛው ባለሁበት በመደንዘዝ ውሥጥ ሆኜ ነው ያሳለፍኩት..ምን አይነት ዘዴ ነው የነገሩኝ...?እንድትመጣልኝ እፈልጋለሁ....በምንም ሆነ በየትኛውም ዘዴ ብትመጣልኝ ለእኔ  ሰርግ ነው...ግን ደግሞ ታምሚያለሁ ብዬ አሥደውዬላት ባትመጣሥ.......?በዛ የተነሣ ውሥጤ ቢቀየማትሥ......?ፍቅሬ ቢቀዘቅዝሥ.......?ፈራሁ.....የምሠሥትለትን ሥሜት እንዳላጣ ፈራሁ...።

እንዴት ሠው  ስቃዩ እንዳይድንለት ይፈራል....?ከእሷ ጋር ያለኝ ፍቅር ማለት ለኔ ስቃይና ጣር ነው የሆነብኝ ....እና ተሳክቶልኝ ቢተወኝ ..ከፍቅሯ ብፈወሥና ከ ሥቃዬ ብገላገል ምኑ ነው ክፋቱ.......?

እረ ከነ ሥቃዬ ለዘላለም ልኑር...ብዙ ደሥታዎች በሥቃዩች የታጠሩና የተለወሡ ናቸው...ሰው ቃሪያ ሲኮረሽም እየለበለበውና እያቃጠለው ቢሆንም የምግብ ጣእም ግን ይጨምርለታል..የጂጂ ፍቅርም ለእኔ እንደዛ ነው የሆነብኝ...ፍቅሯ ልክ እንደሚጠጣ የሚያቃጥል...ነገር ግን በኑሮዬ ላይ ስውር ጣእም ያለው ደሥታ የነሠነሠብኝ ነው።

ለማንኛውም ከብዙ ማሠብና ውዝግብ በሁዋላ ወሠንኩ...የመጣው ይምጣ ብዬ ወሠንኩ....አንድ የሥራ ባልደረባዬ የሆነች እንሥት ፓሊሥን ጠራዋትና ነገርኳት....እየሳቀችብኝ ሥልኩን ተቀበለችኝ.... ደወለችና ታምሜ ሆሥፒታል እንደገባሁ ነገረቻት....ኮሥተር ብላ ነገረቻት...።

ሌላውን ነገር ያው ከእሷ ጋር ሥለነበራችሁ ዝርዝር ታሪኩን ከእኔ በተሻለ ታውቁታላችሁ...

ወደ እኔ እየመጣችና ጉዞ እንደጀመረች ያበሰሩኝ ሽማግሌዎች ናቸው....ከዛ ምን ልንገራችሁ..ሰማይን የጨበጥኩ ጨረቃን የረገጥኩ ነው የመሠለኝ..የምሆነውን አጣሁ...

አሁን ከሁለት ጓደኞቼ ጋር ፊንጫ እገኛለሁ....አዎ መኪና ውሥጥ ሆኜ መድረሷን አይቻለሁ...አቤት ሳያት እንዴት ልቤ ስንጥቅ እንዳለ...ልክ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዳየሁዋት ሁሉ...ከመኪናዬ ወርጄ ወደ እሷ ለመንደርደር ቃጥቶኝ ነበር...በግድ ነው እራሴን ያረጋጋሁት..እሷ በዚህን ሰአት ሆሥፒታል እንዳለሁ ነው የምታውቀው...

አዎ አሁን መኪናቸውን ዳር አሥይዘው በማቆም ሥልክ እያወራች ነው...ጨርሳ ዘጋችው።ደግሞ እንዴት ቆንጅዬ ሆናለች...ቀሚሥ ነው የለበሠችው..እኔ ገዝቼላት የነበረውን ቀሚሥ..እኔን እራሤን የለበሠችኝ ነው የመሠለኝ...ደሥ አለኝ...አዎ ወደ እኔ ሥትመጣ እኔ የገዛሁላትን ልብሥ ለብሣ መምጣቷ እኔን ለማሥደሠት ያላትን ፍላጎት ያሳያል..አዎ ሽማግሌው ትክክል ናቸው ታፈቅረኛለች....ከብዙ መወዛገብ በሁዋላ መኪናቸውን ወደ አንዱ ሆቴል አሥገቡት...የእኛም መኪና ከሁዋላ ተከተላቸው...አልጋ ሲይዙ ከመኪናችን ሳንወርድ እያየናቸው ነው...ክፍሏ ገብታ ሥትዘጋ ሁሉ እያየዋት ነበር...

ከዛ በላይ መጠበቅ አልተቻለኝም...ጓደኞቼን እዛው መኪና ውሥጥ ጎልቼ ወጣሁ..ወደ ክፍሏ ተንቀሳቀሥኩ..ደረሥኩና አንኳኳሁ...ᐸᐸማነው....?>>

ᐸᐸመታወቂያ>>አልኩ ድምጼን ጎርነን አድርጌ....

ከተወሠነ ሠከንድ መንገዳገድ በሁዋላ ተከፈተᐸᐸእፊቷ ተገተርኩ..ነገሬም አላለችኝ..ቀናም ብላ ሣታየኝ መታወቂያዋን አቀበለችኝ...

ᐸᐸአይታይም>>ብዬ ወደ ውሥጥ ገባሁ...ግራ በመጋባት ቀና ብላ አየችኝ...ወደ ሁዋላዋ ሸሸች

....አይኖቿን ጨፈነች...ገለጠች...መልሳ ጨፈነች...ነገረ ሥራዋ ሥላላማረኝ ለማንኛውም ብዬ በራፉን ዘጋሁት...ዋይይይይይይ....>>ጆሮዋን በሁለት እጇ ደፍና አንባረቀችው....መልሼ እኔው ደነገጥኩ..ቶሎ ብዬ አፏን በመዳፌ ደፈንኩት..ከውጭ የእግር ኮቴ...የመሯሯጥ ድምጽ ይሠማኛል...አዎ ትክክል ነኝ...በራፉ ተንኳኳᐸᐸምንድነው ጩኸቱ....?ችግር አለ እንዴ...?>>

ᐸᐸአይ ሠላም ነው..እቃ ወድቆብን ነው...ችግር የለም>>አፌ ላይ የመጣልኝን መልሥ ሰጠዋቸው..

እግዜር ይሥጣቸው በቀላሉ አምነውኝ ተመለሡ...እሷ ግን ትቀጠቅጠኝ ጀመር...በጥፊ...ደረቴ በጡጫ..ወደ ራሴ አፍኜ ጨምቄ አቀፍኳትᐸᐸደደብ ነህ...እንዴት እንደዚህ ታደርገኛለህ......?እንዴት እንዲህ ታሠቃየኛለህ.....?እንዴት እንደዚህ ታሥደነግጠኛለህ...?>>አለቀሠች...አለቀሠችኮ!!!አንገቴ ሥር ተወሽቃ የምታፈሠው እንባ ትካሻዬ ላይ እየነጠረ ወደ ገላዬ ሲሰርግ ቅዝቃዜው ይታወቀኛል...በእኔም አይኖች ውሥጥ እንባ ግጥም አለ...በዚህ መጠን ማፍቀር.....በዚህ መጠን መፈቀር....በዚህ አይነት መንሠፍሠፍ መተቃቀፍ...በዚህ አይነት ሥሜት እንባ ማፍሠሥ..ጌታ ሆይ ይሄን ደሥታ ህልም እንዳታደርገው...ህልም ከሆነ ደግሞ እንድነቃ አታድርግ...በቃ እሷ ከሌለችበት የእውነት ህይወት ከእሷ ጋር ባንድ ላይ የህልም አለም ውሥጥ ለዘላለሙ ብጠፋ ይሻለኛል>>ጨምቄ እንዳቀፍኳት ለአምላኬ ያሠማሁት ጸሎት ነበር....ከልብ የመነጨ የማጣት ፍርሃት የወለደው ፀሎት......አሁን ተኝቻለሁ እዚህ ቤት እዚህ አልጋ ላይ ማደር ከጀመርኩ 3 ቀን ሆነኝ።

መኝታ ቤቷ ሶስት በሶስት የሆነች የምታምር ክፍል ሥትሆን በውሥጧ መካከለኛ ሥፋት ያለው መዝቦልድ አልጋ ተዘርግቶበታል።

ሻንቦ ከተማን ወድጃታለሁ ብላችሁ ውሸት ይሆንብኛል ከተማዋ አንድ እድሜዋን በሙሉ ፒያሳ ለኖረች የአራዳ ልጅ ምንም የከተማነት ጣእም የሌላት እልም ያለች የገጠር መንደር ነች ብትል ጉረኛ ልትባል አይገባም ለነገሩ እኔ እንደዛ አልተሠማኝም ምክንያቱም ብዙም ለውጪው ማለቴ ለከተማዋ ሥፋትና ጥራት ትኩረት አልሠጠውም....ቤቱን ግን ወድጄዋለሁ ብቻ አይገልጸውም..ልጅቷን...አሮጊቷንሥ ቢሆን አሮጊቷ ያልኳችሁ የዋቅቶላን እናት ነው...በጣም ጥሩና ደግ አዛውንት ናቸው..ከአማርኛ ይልቅ ኦሮምኛ ቋንቋ ይቀናቸዋል...እኔም ቋንቋውን የማውቅ ይመሥላቸውና አንዳንዴ ድንግርግሬን ያወጡታል...

<<ልጄ ከቤተሠቦችሽ ጠፍተሽ ነ...?>>ይጠይቁኛል በመጨነቅ..

በእሳቸው እይታ እኔ ገና ክፉና ደጉን ለይቼ የማላውቅ አንድ ፍሬ ጨቅላ ልጃገረድ ነኝ።..ይህን ያልኩት ከምንም ተነሥቼ አይደለም...ከመጣሁ እለት ጀምሮ ከቤተሠብ ጋር አምሽቼ ለብቻዬ ለመተኛት እዚህች አሁን ወዳለሁባት ክፍል መግባቴ ከመፍራቴ...ጨዋ ከመሆኔ...ድንግልናዬን እንዲሁ በቀልድ ላለማሥወሠድ የማደርገው ጥረት አድርገው ነው የወሠዱት...እና ይሄ ደግሞ በእሣቸው ከፍተኛ ክብር አሰጥቶኛል።

<<ጎሽ ልጄ እንደዘመኑ ልጆች አይደለሽም>>አሉኝ...ፈገግ አልኩ..እውነትም ከዘመኑ ልጆች በተቃራኒ እየተሽኮረመምኩ በውሥጤ <<አልሠሜን ግባ በሉት...>>እያልኩ..በነገራችን ላይ እዚህ ሻንቡ ከተማ ከገባሁና እዚህ ቤት ከረገጥኩበት ቀን ጀምሮ አንገት ደፊ ተቅለሥላሽና በጣም ጭምት ልጅ ወጥቶኛል...ለራሤም እሥኪገርመኝ ድረሥ....መቼሥ ፒያሣ ላይ የሚያውቀኝ ሠው አሁን የሰሞኑን ሁኔታዬን ቢመለከት ምን አይነት አሥመሳይ ልጅ ነች ብሎ አሥተያየት መሥጠቱ አይቀርም...እኔ ግን ለማሥመሠል ብዬ ምንም የሞከርኩት ነገር የለም...ግን በቃ ውሥጤ ነው እንደዛ እንድሆን የሚገፋፋኝ..ልንቀልቀል ብልም እግሬ አይፈጥንልኝም...ልለፍልፍ ብልም አንደበቴ አይላቀቅልኝም...ልፍጠጥ ብልም ቅንድቤ አይበለጠጥልኝም...አሮጊቷ በሠሞኑ አብሮነታችን ልጃቸው ጥሎን ሲወጣ ያወሩኛል...<<አይዞሽ ልጄ...ክብሯን የምትጠብቅ ልጅ እወዳለሁ...ከጋብቻ በፊት እንዲች ብለሽ>>..በገዛ ልጃቸው ላይ ያሣድሙበታል...ወደድኳቸው...በውሥጤ እያፈርኩ ወደድኳቸው..ምነው እሳቸው የ ሳሏትን ልጅ ሆኜ ቢሆን ኖሮ ሥል እየተመኘሁ....

ልጃቸውን የማግባት ፍላጎት የለኝም...ግን እሳቸው እናቴ እንዲሆኑ እፈልጋለሁ..አይ አሁንም ይሄ ዙሪያ ጥምጥም መዞር አልተወኝም...እውነት ጂጂ ይቅርታ ሻንቡ ከመጣሁ ጀምሮ ከማገኛቸው አዳዲሥ ሠዎች ጋር ሥተዋወቅ እጅጋየሁ እባላለሁ....እጅጋየሁ ዜና ብዬ ሙሉ ሥሜን በወጉ መናገር ጀምሪያለሁ......ያው ዜና ትክክለኛ አባቴ እንዳልሆነ ታውቃላችሁ...ዜና ጋሽ ዜና ናቸው...ከእኔ ሥም ቀጥሎ ለመጠራት ብቃቱም መብቱም ያለው ይሄ ዜና የሚሉት ሥም ነው....በእኔ ህይወት ውሥጥ ድርሻ ያለው...እና ወደ ነገሬ ልመለሥና <<እጅጋየሁ በእውነት ዋቅቶላን ማግባት አትፈልጊም....?የዚህ ቤት እማወራ ለመሆን ፍላጎት የለሽም...?ብዬ እራሤኑ ሥጠይቅ ....<<በፍጹም..>>ብዬ ለራሴ ልመልሥ አፌን እከፍትና መግጠም ያቅተኛል...ያንቀኛል....ቃላቱን ማሥፈንጠር ያቅተኛል።

ውይ የመኝታ ቤቱን በር የሚቧጭር ነገር አለ ...ምንድነው ሰአቴን አየሁ አራት ሠአት ተኩል ነው.....እረ የመንኳኳት አይነት ድምጽ እየተሠማኝ ነው...ደካማ የበር መንካት አይነት ድምጽ...ድምጹ ሌላ ክፍል እንዳይሠማ የመፍራት አይነት ስሜት ያለው.....<<ምን አይነት ድመት ነች ይሄን ከመሠለ ሃሣቤ መንጭቃ የምታወጣኝ.....?>>

እየተነጫነጭኩ ከወልጋዬ ወረድኩ...እርቃኔን ነኝ።በሠውነቴ ላይ ያለው ሠማያዊ ፓንቴ ብቻ ነው..በራፉን ቀሥ ብዬ ከፈትኩት...ድመቷን ላባርራት...<<በአራዳው ጊዩርጊሥ..!!!በራፉ ላይ ማን እንደተገተረ ታውቃላችሁ.....?እሥኪ ገምቱ>>አትቸኩሉ አላገ ኛችሁትም...ማለቴ ግምታችሁ ትክክል አይደለም...ዋቅቶላ መሥሏችሁ ነበር አይደል....?በራፍ ላይ የቆመችው የዋቅቶላ ትንሽ እርግብ ነች...በእንቅልፍ የደከሙ አይኖቿን በዛ የሚያምር ሚጢጢ እጇ እያሻሸች በሌላ እጇ በራፉን ሥትቧጥጥ የነበረችው......

<<ቦንቱ ምን ሆነሽ ነው...?>>

<<እማ እማ...>>እጆቿን እንደ ምርኮኛ ግራና ቀኝ አንከርፍፋ...እንዳቅፋት መሆኑ ነው>> በርከክ ብዬ አቀፍኳት እና ወደ ውሥጥ ገባሁ..በራፉን መለሥ አደረኩትና ወደ መኝታዬ ይዣት ወጣሁ...ክንዴን ተንተርሳ  ጡቶቼ መካከል ገብታ ውሽቅ አለች...

<<ምነው የኔ ጣፋጭ....?ጸጉሯን እያሻሸሁላት ..ምንም አልመለሠችልኝም..ጭራሽ አይኖቿን ከደነች...በውሥጤ የተሠማኝን ሥሜት ልነግራችሁ አልችልም...እንዴት እግዜር እንዲህ ደግ ሊሆን ቻለ......?

እሱ መቼሥ ሲሰጥ ስስት የለበትም።...እድሜዋን መሉ ሥትገፋና ሥትበደል የነበረች..ዘር ማንዘር ያልነበራት ወፍ ዘራሽ ልጅ በአንዴ ሙሉ ቤተሠብ ሲሰጣት ይሄ መቼሥ መመረቅ ነው....?እሥከ መቼ ይሆን ይሄ ደሥታ ከእኔ ጋር የሚቀጥለው....?

...የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና እኔ የሚያበቃልኝ ይሄንን አሁን የተሠ ጠኝን ፍቅር የተነጠቅኩ ቀን ነው።...

እሥከዛሬ ዋቅቶላ በምን ያህል መጠን እንዳፈቀረኝ ታውቃላችሁ...እናቱም እንዴት እንደተቀበሉኝ በመጠኑም ቢሆን ነግሬያችሆለሁ...የዚህችን ህጻን ያህል ግን የወደደኝ የለም...እንደመጣሁ ነው የተለጠፈችብኝ..ልክ ለብዙ ጊዜ እንደምታውቀኝና ሥትጠብቀኝ እንደኖረች አይነት..ቀኑን ሙሉ ወደ ሣሎን ሥሄድ ሥትከተለኝ.....ኩሽና ሥገባ አብራኝ ሥትገባ..ይገርማችሁዋል ሽንት ቤት ሥገባ እንኳን አታምነኝም<<...እማ...>>ሥትለኝ

የእውነት እናቷ የሆንኩ ነው የሚመሥለኝ...አሁን ከአንድ ሠአት በፉት እራት እየበላን ሣለ ክንዴ ላይ ነበረ እንቅልፍ የወሠዳት...ከዛ ቀሥ ብዬ ከአባቷ አልጋ ላይ አሥተካክዬ አሥተኝቼያት ነበር የመጣሁት...ከእሡ ጋር ሥለምትተኛ...ይሄው ስትነቃ እና ሥታጣኝ መጣች.....

እና ታዲያ መጨረሻዬ እንዴት ነው የሚሆነው......?እዚህ ቤት ውሥጥ ነገን ብቻ ነው የምውለው...የጀመርኩትን ነገር ለመጨረሥ ወደ አዲስ አበባ እመለሳለሁ...እቅዴን ለማሣካት ደግሞ ቢያንሥ አንድ ወር እዛው መቆየት ይጠበቅብኛል....በዛ ላይ አደጋ ሊያጋጥመኝ ይችላል...ልታሠርም እችላለሁ...

እና እንዴት ነው የምችለው......?እንዴት ነው ከዚህች መላእክ ተለይቼ የምኖረው......?እና ቢቀርብኝሥ.....?አዎ ቢቀርብኝሥ....ሮማንን ለመበቀል መባከኑ ቢቀርብኝ...እርግፍ አድርጌ ብተወው...ይቅር ብላት.....?

<<አይ ወይዘሪት ጂጂ ይሄማ ደካማነት ነው....ለአዕምሮሽ ፊት አትሥጪ...ያቺን አውሬ በቂ ቅጣት ሳትሰጪያት እና ከዚህች ምድር ሳታሰናብችያት ወደ ሁዋላ ብትይ የእናትሽ የሙት መንፈሥም ይቅር አይልሽም>>እራሴን ገሰጽኩ...አበረታሁ..አዎ በእቅዴ መሠረት ነገን ብቻ ውዬ መሄድ አለብኝ...አዎ ጠላቴን ለመበቀል..ከዚህ የበለጠ ፍቅር ቢሰጠኝ እንኳን እሰዋዋለሁ እንጂ አልታለልም..ሮማን በምትኖርበት ምድር ላይ እኔ መኖር አልፈልግም..የእኔ አዲሥ ህይወት መጀመር ያለበት በእሷ ሞት ላይ ነው....ውሳኔዬን አደሥኩ.....ዛሬ ምን አይነት ቀን ነው..አሁንም ሳልቀረቅር የረሳሁት በራፍ በዝግታ ተከፈተ.....

ቀና ብዬ አየሁ...አሁን ደግሞ አባትዬው ነው..ዋቅቶላ።አንገቱን አስግጎ ወደ ውሥጥ እያየ ነው...

<<አንቺ ነሽ የወሠድሻት....?>>በማለት ጠየቀኝ.....ብንን ሲልና ልጁን ከጎኑ ሲያጣት ነው ፍለጋ የመጣው...አለመተኛቴን ሲያውቅ ወደ ውሥጥ ገባ

<<አይ...እራሷ ነች የመጣችው>>

<<ወይ ጉዴ...የእኔ ይሁን ልጄን ደግሞ ምን አሥነካሽብኝ....?>>እያለኝ መጣና አልጋው ጠርዝ ላይ አረፍ አለ..

<<ቀናህ እንዴ...?>>

<<አይ አልቀናሁም...ፈራሁ እንጂ>>ሲል መለሠልኝ።..አልመለሥኩለትም...ዝም አልኩት...ምክንያቱም እሱ ብቻ ሳይሆን እኔም ፈርቼያለሁ....ነገ በጣም ያሥፈራል።

.....ከተወሠነ በዝምታ የታገዘ መተከዝ በሁዋላ ተነሳ....ወደ ውጭ መራመድ ጀመረ....<<አይዞህ አታሥብ ከእኔ ጋር ይመቻታል>>አልኩት...ለልጁ እንዳይጨነቅ በራፉ ጋር ደረሠና ከፍቶ ይወጣል ብዬ ሥጠብቅ..ቀረቀረውና ተመልሶ መጣ...ደነገጥኩ..ልክ እሥከዛሬ አብሬው ተኝቼ እንደማላውቅ ሁሉ ደነገጥኩ...ልክ ልጃገረድ እንደሆንኩ አይነት...ልክ ተሳሥቶ እንዳያሣሥተኝ እንደፈራሁ አይነት...

<<ምን እየሰራህ ነው....?>>

<<እኔም ካንቺ ጋር ብተኛ ይመቸኛል....?>>

<<አይሆንም...>>

<<ለምን.....?>>

<<አይሆንማ እናትህ ምን ይሉናል....?>>

<<ምንም አትለንም....አብረው ተኙ ብቻ ነው የምትለን>>አልጋው ላይ ወጣና ከሁዋላዬ ተሻግሮ ብርድ ልብሱን ገልጦ ገባ......

<<ቀሺም ነህ.....እናትህ ሌላ ነገር እንዲያሥቡና እንዲደብራቸው አልፈልግም>>

<<አትነጫነጪ...ትንሽ ተኝቼ እሄድልሻለሁ>>ወደኔ ዞሮ አቀፈኝ...እኔ ፊቴን ወደ ቦንቱ ነው ያዞርኩት...እሱ እኔን እኔ ደግሞ የእሱን ልጅ እንዳቀፍን በፀጥታ ተዋጥን....ለረጅም ደቂቃ በፀጥታ....

<<ተኛሽ እንዴ...?>>አለኝ......ምንም አልመለሥኩለትም....እንደውም ቀና ብሎ ካየኝ ብዬ አይኖቼን ጨፈንኩ...ማውራት አልፈለኩም...ከጎኔ ሥለተኛ ደሥ ብሎኛል ግን ደግሞ ፈርቼያለሁ...እናቱ ቢያውቁሥ........?እንደዛ መክረውኝ.....እንደዛ አሥጠንቅቀውኝ.....ድንግልናዬን ላሥወሥድ....?የራሴው ቀልድ ለራሴው ፈገግ አሰኘኝ...

እንደገመትኩት ቀና ብሎ አንገቱን ወደፊት አሰገገና አየኝ....መተኛቴን ሲያረጋግጥ ወይም የተኛሁ ሲመሥለው ተንጠራራና መብራቱን አጠፋው......

እኔ ቀድሜ ከተኛሁበት ወጥቶ ይሄዳል ብዬ ነበረ ያሰብኩት እሱ ጭራሽ ለብሶ የመጣውን ቁምጣ እያወለቀ ነው.....ተመልሶ ተኛ....አቀፈኝ....መቀመጫዬ ላይ ተለጥፎ አቀፈኝ...መላ አካሉ አካሌ ላይ ተጣበቀ...እንዲህ ሲሆን የመጀመሪያ ቀናችን ነው....ሁለታችንም እርቃን ሆነን እንዲህ ተኝተን አናውቅም....የውሸት ማንኮራፋቴን ቀጠልኩ.....የውሸት ማንኮራፋቴን ቀጠልኩ...አዎ ማንኮራፋት አለብኝ...ምክንያቱም ጥልቅ እንቅልፍ ውሥጥ አይደለሁ ያለሁት...እሱ ይበልጥ ተጣበቀብኝ...እና ጨነቀኝ...በራሴ መተማመንም አቃተኝ...ለምንድነው ይሞቀኝ የጀመረው......?ደግሞ ምን አለ ጆሮ ግንዴ ላይ ባይተነፍሥብኝ...የትንፋሹ ሙቀት ቆዳዬ ላይ ብቻ ተበትኖ አይጠፋም ወደ ውሥጤ ሰርጎ ከደም ስሬ ጋር በመቀላቀል ወደ ጠቅላላ ሠውነቴ ሲሰራጭና የውሥጥ ሙቀቴን ሲያንረው ይታወቀኛል...

ቀኝ እጁ ከትካሻዬ ላይ ተንሸራቶ ጡቴ ላይ አረፈ...የጡቴን ጫፍ በስሱ ያሻሸው ጀመር....እንዴ ምን አባቱ እያደረገ ነው........?ተው እንዳልለው ደግሞ ተኝቻለሁ...እያንኮራፋሁ ነው...ምን ይሻለኛል....እረ ፓንቴም ሊቀደድ ነው...ምን አይነት ደረቅ ችካል ነው የሚሠረሥረኝ........?አሁንማ መንቃት አለብኝ.....አዎ ነቅቼ አይኖቼን ከፍቼ ይሄን ሠውዬ ከዚህ ቤት አሽቀንጥሬ ማሥወጣት አለብኝ....ግን አልቻልኩም.....እንዴት አድርጌ ልንቃ...?ይገርማል አይደል ሠው ከውሸት እንቅልፉ መንቃት ሲያቅተው ይሄ እንኳን ለሠሚውም ለእኔም ለእራሤ እንቆቅልሽ ነው....ግን የእውነቴን ነው..ለነገሩ በህይወት ውሥጥም የእውነት ከተኙት ይልቅ ለማሥመሠል ያሸለቡት ናቸው ዋናዎቹ እንቅፋቶች......

........አይኖቼን ለመግለጽ እየፈለኩ ነው እንቢ ያለኝ...እጆቼን ለማነቃነቅ እየፈለኩ ነው አልታዘዝ ያሉኝ.....አንደበቴን እራሡ አላቅቄ ተወኝ ማለት አልቻልኩም....እንዴ ጉድ ፈላ.....ጉድ ፈላ....ምን ተፈጠረ መሠላችሁ....የጠረጠርኩት ብቻ ሆኖ እንዳይሆን.....?የሆነ ሙቀት ነገር ጭኖቼ መካከል ተሠማኝ...እርጥበት ነገር...።

እረ ለወሬ አትቸኩሉ እሡ ረጭቶ አይደለም እኔው ነኝ በራሤው የረጣጠብኩት....።

....እንዲህ አይነት መሸነፍ እንዲህ አይነት መበላሸትማ አይደረግም...እንደምንም ከራሴ ታግዬ አይኖቼን ገለጥኩ...እጄን አንቀሳቀስኩና ብርድ ልብሱን ከላዬ ላይ አሽቀነጠርኩ...ቀሥ ብዬ ጥልቅ እንቅልፍ ላይ የምትገኘውን ቦንቱን ከእጄ ላይ አወረድኩና እንዳትነቃ በጥንቃቄ ትራሱ ላይ አሥተካክዬ አሥተኛዋት...ከዛ ቁጭ አልኩ...እሱ በፍራቻ አፈግፍጎ የግድግዳውን ጥግ ይዟል...

ቀኝ እጄን ወደ ጭኔ ላኩ...በፓንቴ ውሥጥ እጆቼን ሠድጄ ብልቴን ፈተሽኩ...አዎ በትክክል ዝናብ እንዳጥለቀለቀው መረሬ መሬት በፈሳሽ ላቁጧል...ይሄ ቀላል እንዳይመሥላችሁ...ይሄ በህይወቴ ገጥሞኝ የማያውቅ ክሥተት ነው..ይሄ ማለትኮ የእውነት በዚህ እሥሬ በተኛው ወንድ ለመሸነፍ ተዘጋጅቼያለሁ ማለት ነው...

....የእውነት ወሲብ በሚሉት አዚም ለመደሠት ቋምጪያለሁ ማለት ነው....።

መብራቱን ተንጠራርቼ አበራሁት..እርቃን ገላውን ኩርምትምት ብሎ ምን ይፈጠር ይሆን.....?በሚል ፍራቻ እየተቁለጨለጨች ያየኛል...ዝላይና ተጠምጠሚበት...እላዩ ላይ ወጥተሽ በደሥታ ጨፍሪበት...ከንፈሩን በከንፈርሽ ግመጪው...እነዚህንና የመሳሰሉትን ብዙ ብዙ ሥሜቶችን በአንዴ ሥትከፋፍይና ሥትሸራርፊ አድርጊ የሚል ሥሜት ቀሠፈኝ....ያደረኩት ግን ተቃራኒውን ነው...

<<ተነስ ውጣልኝ...አሁኑኑ ውጣልኝ>>አይኔን አጉረጥርጬ

......ምንም አልተከራከረኝም ሹክክ ብሎ ተነሳና ከወልጋው ላይ ወረደ አወላልቆ እዚህም እዚያም የወረወራቸውን ልብሶቹን ሰበሰበ...እንደ ህጻን ልጅ በጉያው ወሽቆ እርቃኑን ክፍሉን ለቆ ወጣ....

<<በቃ ተመለሥ>>ልለው ዳድቶኝ ነበር.....ቃላቱ ግን ከአንደበቴ ሊሾልክ አልቻለም...>>ተነሳሁና በሩን ቀረቀርኩት..እንባዬን አፈሠሥኩ...አዎ ልክ እንደበቀደም ለታው ዛሬም አለቀሥኩ

..ወደ መኝታዬ ተመለሥኩ..እንዲሄድ አልነበረም የፈለኩት<<…ምን አባሽ ሆንሽ...አልሄድም...እንዲጋፈጠኝና እንዲያሸንፈኝ....በቀላሉ ተሸንፎ ጥሎኝ ሲሄድ ውሥጤ ሥብርብር አለ.....እንዴት እንዲህ ያደርገኛል....?

መንጋት አይበለው ነጋ....የዋቅቶላ እናት ጣት የሚያሥቆረ ጥም ጨጨብሳ ሰርተው ከእርጎ ጋር ቁርሥ አቀረቡልን...በላን...በተለይ እኔ ደሥ ብሎኝና ጣፍጦኝ ነው የበላሁት...ዛሬ ቅዳሜ ሥለሆነ ዋቅቶላ ሥራ አልሄድም ብሎ በቢጃማ ነው ያለው...ሁለታችንም አይን ላይን መተያየት ፈርተናል..

የእሱን አላውቅም እኔ ግን ከማታው ነገር ይልቅ ዛሬ የሚሆነው ነው እያሥጨነቀኝ ያለው...ነገ እንደምሄድ አያውቅም...እንዴት አድርጌ እንደምነግረው ጨንቆኛል....እንዴት ብዬ ምንሥ ተናግሬ አሳምነዋለሁ......?ነው ወይሥ ዝም ብዬ ለሊት በተኙበት ሹልክ ብዬ ልሂድ...እንዲህ ባደርግ ደግሞ ጥሩ አይሆንም ..<<እረ ምናባቱ እነግረዋለሁ..አላገባሁት ምን አጨናነቀኝ..............................እራሴን አበረታሁ..ግን ምንም ነገር ለእሱ ከመንገሬ በፊት ቆይ በመጀመሪያ እነ ስንዝሮ ጋር ልደውል..ሁለተኛውን ተልእኮ እንዲፈጽሙ ትናንትና ፍቃድ ሰጥቺያቸው ነበር...

ሁለተኛው የበቀል ተልእኳችን ቀለል ያለ ሥለሆነ እኔም ባልኖር ችግር የለውም ብዬ ሥላመንኩ...ዛሬ በለሊት ሶስቱም የሮማንን ቤት ሰብረው ገብተው...ከአልጋዋ ጋር ጠፍረው አሥረዋት...ፊት ለፊቷ ያቺን የምትወዳትን ድመቷን (ሰው በእሷ አሠርታ ነው እንዲህ ከተራ ሽርሙጥና ተነሥታ ያለፈላት እያሉ ያሟታል)...እና ድመቷን አይኗ እያየ እንዲታረድባትና በድመቷ ደም ሰውነቷን እንዲያጥቧት...በቤቱ መቃጠል በውሥጧ የነገሠውን ፍርሃት ይበልጥ ነፍሷ ድረሥ እንዲሠማትና እንዲያንቀጠቅጣት...የምትደበቅበት ጥግ እንድታጣ....በቁሟ መባነን እንድትጀምር...የራሷ ጥላ እንዲሸክካት...አዎ ይሄን ማድረግ ደግሞ ለእነሱ በጣም ቀላል ነው።...

.....ከሶሥተኛው እሥከ አምሥተኛው ወይም መጨረሻው የሚደረገው ተልእኮ ግን በጣም ውሥብሥብና አደገኛ ሥለሆነ የግድ እኔን ይፈልጋል...ደግሞ እያንዳንዷን ስቃዮን በአይኔ ማየት አለብኝ..በእኔ ሥቃይ ውሥጥ ለአመታት ደሥታ ሥትሸምት እንደኖረች ሁሉ አሁንም እኔ በተራዬ ከእሷ ስቃይ በሚቀዳ ሳቅ ዘና ማለት እፈልጋለሁ።...

.....ሥልኬን ይዤ ከእነዋቅቶላ ተለይቼ በጓሮ በር ወደ ውጭ ወጣሁ...ደወልኩ ሥንዝሮ ጋር..ያው ነገሮችን የማብራራት እና አሳምሮ የማውራት ችሎታ የተፈጥሮ ሥጦታው ነው ብዬ ነው እሱ ጋር መደወል የሚቀናኝ....

<<ሄሎ ስንዝሮ>>

<<ሄሎ ወፏ...ላጮህልሽ ስል ነው የቀደምሽኝ>>

<<የለሊቱ ሚሽን እንዴት ሆነላችሁ....?>>ቀጥታ መሥማት ወደምፈልገው ርእሥ ወሠድኩት

<<ሚሽኑ ባክሽ ከሽፏል>>ክው ነው ያልኩት

<<ምን ተፈጠረ....?ምን ሆናችሁ....? ማን ታሠረ.....?>>

<<እረ እንደዛ አይነት ነገር አልተከሠተም>>

<<እና ታዲያ......?>>

<<ሴትዮሽ ተሠውራለች...>>

<<ተሰውራለች ስትል.....?>>

<<ሁለት ቀን ሆናት በአዲሥ አበባ ውሥጥ የትም ቦታ አልታየችም...በተለይ የፒያሳን አንድ ጓዳ ጎድጓዳ አልቀረንም...>>

<<እና......?>>

<<እናማ እየፈለግናት ነው>>

<<የትም መጥፋት የለባትም...እናቷ ሆድም ብትገባ ጎትቼ አወጣታለሁ...ብትሞት እንኳን ከሲኦልም ቢሆን እመልሳታለሁ...ከእኔ ማምለጥ አትችልም...>>

እራሴን መቆጣጠር አቅቶኝ ከጣሪያ በላይ እየጮህኩ ነው የማወራው....ዋቅቶላ እና አሮጊቷ በጩኸቴ ተደናግጠው ተከታትለው ወደ አለሁበት ቦታ መጡ...ግራ በመጋባት እያዩኝ ነው...አሮጊቷ እንደዛ ጭምት የነበርኩት ልጅ እንዲህ ነብር ሆኜ ስላዩኝ ተደናግጠዋል...ፈርተዋልም

<<ዋቆ....ሙጬዬ ማል ታቴ......?ማልቱ አከነቲ መራቺሴ.....?>> ብለው ሲጠይቁት ሰማሁ....

እሱ እንደፈዘዘ ነው...ምንም አልመለሰላቸውን....እኔም ምን እንዳሉ ለመረዳት አልቻልኩም...

ስልኬን ዘጋሁና ወደ እሱ በማፍጠጥ መናገር ጀመርኩ<<መሄዴ ነው...ነገ መሄድ አለብኝ>>አልኩት....አሁን ንዴት ላይ ሥላለሁ ከይሉኝታ ውጪ ሆኛለሁ...

ለማንም ሥሜት መጨነቅ አልፈለኩም....

<<ልጄ ቤተሠቦችሽ ናቸው ያበሳጩሽ.....?አይዞሽ ያለፍቃዳቸው ወደዚህ ሥለመጣሽ ተናደውብሽ ይሆናል>>በማለት ሊያጽናኑኝ ሞከሩ አሮጊቷ...ውሥጣቸው ያለውን ሥጋት በማንሳት በገባቸው መጠን......

<<እማማ ግድ የለም አያሥቡ ምንም አልሆንም>>

<<አዎ ትክክል....እኔ እያለውልሽማ ምንም አትሆኚም...ይሄ የእኔ ጅልኮ ምኑንም አያውቅ....በእንዲህ አይነት ሁኔታ ከቤተሠቦችሽ ነጥሎ ይዞሽ መምጣት አልነበረበትም....ቀድሞ ቢያማክረኝ ኖሮ ሽማግሌ እልክ ነበ...አይዞሽ አሁንም ይሥተካከላል...በእኔ ይሁንብሽ ከቤተሠቦችሽ እንድትታረቂ አደርጋለሁ....>>

የእሳቸው ማጽናናት ከመጠን በላይ  ተለጥጦ ሊፈነዳ የነበረውን ሥሜቴን አሥተነፈሠው......ተንደርድሬ ወደ እሳቸው ሄድኩና ተጠመጠምኩባቸው<<....እማማ እኔ የሚቆጣ ቤተሠብ የለኝም...እናቴም አባቴም ሞተዋል...>>ተናዘዝኩላቸው...ግን የእናቴሥ እሺ ይሁን ሞታብኛለች ወይም ተገድላብኛለች አባቴ የሞተው መቼ ነው....?የሌለ ነገር እንዴት ሊሞት ይችላል...ለመሞት እንኳ መጀመሪያ ተፈጥሮ መኖርን ይጠይቃል....

<<ያ ዋቅዬ...አይዞሽ እኔ እናት እሆንሻለሁ...>>እያጽናኑኝ ይዘውኝ ወደ ቤት ገቡ....እሱ በፍራቻ እንደተሸበበ ሹክክ ብሎ ከሁዋላ ተከተለን...በዚህ ጊዜ ህጿኗ ቦንቱ አብራን አለመኗሯን ወደድኩት...አክስቷ ነበረች በጥዋት መጥታ ከእቅፌ ፈልቅቃ እያሥለቀሠች የወሰደቻት....እቤት ገብተን ገና ተረጋግተን እንኳን ሳንቀመጥ ሌላ ሥልክ ተደወለልኝ...አየሁት...ጋሽ ዜና ናቸው...

አነሳሁት<<አቤት ጋሼ>>

<<ሰላም ነሽ ልጄ......?>>

<<ሰላም ነኝ>>

<<እንዴት ይዞሻል.....?>>

<<ደህና ነኝ...ነገ እመጣለሁ>>

<<ምን ልትሠሪ......?>>ጠንከር ባለና በሚጋፋ ድምጽ 

<<እንዴት ምን ልትሠሪ....?ወደ ቤቴ ነዋ>>

<<ኤዲያ ምን ቤት አለሽ...ቤት ማለትኮ ድንጋይና ቆርቆሮ ውሥጥ የተከማቸ ቁሳቁስ ያለበት ሥፍራ አይደለም....ያ ቤት ሣይሆን መጋዘን ነው የሚባለው...ቤት ማለት ቤተሠብ ያለበት ቦታ ነው...ሥለዚህ አርፈሽ እዛው ቆዪ ደግሞ ሴትዬዋን ፍለጋ ከሆነ እንዳትለፊ>>ስለ ሴትዬዋ ሲያነሡ ሥሜቴ ተነቃቃ...

<<ምን ሆነች.......?ስለ እሷ የሚያውቁት ነገር አለ.......?>>

<<አምልጣሻለች>>ከንግግራቸው ስረዳ ስላመለጠችኝ የተደሠቱ ይመሥላሉ....ምን ይታወቃል...ሆን ብለው ይሆናል ከኔ ያሥመለጧት

ጥያቄዬን ቀጠልኩ<<ማለት የታባቷ ልትሄድ ትችላለች......?>>

<<ቤቱን ባንቺ ሥም አዙራ...ሶስት ገጽ የይቅርታ ደብዳቤ እኔ ጋር አሥቀምጣልሽ ጨርቄን ማቄን ሳትል ገዳም ብላ ተሠውራለች>>

<<ምን.......?ገዳም....?>>

<<አዎ ገዳም>>

<<እንዴ ሰይጣን ገዳም መግባት ይፈቀድለታል እንዴ....?>>

<<ልጄ መድሃኒትኮ ለበሽተኛ ነው የሚታዘዘው...ገዳም ከአምላክ የመታረቂያ እና ጽድቅን የመፈለጊያ ሥፍራ ከሆነ የሚገባው ለእንደሷ አይነት ሀጥያተኞች ነው ብዬ አሥባለሁ...ጻድቁማ አንዴ ጸድቋል...ሥልኩን ዘግቼ ዝም አልኩ...ምንድነው የማደርገው.....?ምን ይሻለኛል......? የትኛው ገዳም ይሆን የገባችው......?የትስ ብትገባ መቼሥ ገዳም ድረሥ ተከታትዬ አላጠፋት...ቀና ብዬ ዋቅቶላን አየሁት አይን አይኔን ሲያየኝ ስለነበር ተጋጨን... ከዋቅቶላ ጋር ስለሚኖረኝ የወደፊት የፍቅር ህይወትና ለቦንቱም ምን አይነት እናት እንደምሆንላት እያሰብኩ ፈገግ አልኩለት....... እሱም ከንፈሩን ገለጥ አድርጎ ከነጫጭ ጥርሶቹ ከፊሎቹን አስመለከተኝ.....

.

.

ከሳምንታት በሁዋላ እጅጋየሁ ዜና(ወፏ) የኔ የምትለው የራሷ ቤተሰብ ኖራት።የዋቅቶላ ህጋዊ ባለቤትና የቦንቱ እናት በመሆን አዲሱን ህይወቷን ምእራፍ አንድ ብላ ጀመረች። አዎ እግዜር ፍቅርን ከመዳፉ ፈልቅቆ በዋቅቶላ አሥመሥሎ ልቧ ውሥጥ አሰረገው..በመጨረሻም የመጨረሻውን ደስታ..ከአጽናፍ አጽናፍ የሚናኝ ደስታ በዋቅቶላ ጎጆ ውስጥ አገኘችው...ከወራቶች ምናልባትም ከአመታት በሁዋላ ለቦንቱ ታናሽ እህትም ይኖራት ይሆናል።

.

.

ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም..በሆድህ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ!!!

.

.

.

/////🎀 ተፈፀመ 🎀//////


የፒያሳዋ ወፍ ክፍል ሁለት

የፒያሳዋ ወፍ
ክፍል ሁለትImage result for የፒያሳዋ ወፍ ‹‹ምን አደረግሺው?›› ‹‹ዝርዝሩ ምንም አያደርግልህም ..ግን እድሜ ልኩን እንደተሸማቀቀ እና ምነው ባላደረግኩት ኖሮ እያለ ሲፀፀት እንዲኖር ነው የፈረድኩበት…ቀን ጠብቄ ከሶስት ወር ቡኃላ የዘር ፍሬውን ነው ያፈረጥኩለት ..ዕድሜ ልኩን ሴት ስር እንዳይደርስ….ለእሱ የሴትን ገላ ማቀፍ.. በሴት ፀጋ መደሰት አይገባውም…… ከዚህ በላይ ታሪኳን ለእኔ በመንገር ይበልጥ በውስጥ ሀዘኗ ምርቃዜ እንድትሰቃይ አልፈለኩም ….ከአልጋው ላይ ያለውን አልጋ ልብስ አነሳውና እርቃን ሰውናቷን አለባስኳትና አልጋው ላይ ይዤት ወጣው ..ይዤት ተኛው..በአልጋ ልብሱ አሷንም አራሴንም ጠቅልዬ ..፡፡ ባለፉት ሶስት ቀናቶች ካቀፍኳት በላይ አቅፌያት …አስከዛሬ ካዘንኩላት በላይ አዝኜላት… በእነዚህ ሶስት ቀኖች ከወደድኳት በላይ ወድጄያለት ጭምቅ አድርጌት ውስጤ ሸሽጌት.. ሁሉን ነገር አረስቼ ዓለምን ሁሉ ዘንግቼ ስለእሷብቻ እያሰላሰልኩ በፀጥታ ውስጥ ተዋጥኩ……እሷም በድካምና በእፎይታ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ውስጥ ገባች….እኔም….ጩኸቷ ነው ከእንቅልፌ ያባነነኝ…‹‹ተነሳ..ተነሳ›› ወታደር አይደለው… ከመቅፅበት ከእንቅልፌ ተስፈንጥሬ ተነሳውና ወለሉ ላይ ቆምኩ…. ‹‹….ምንድነው.?.ምን ሆነሽ…?››ጩኸቷ እና ድንጋጤዋ የሆነ በቃ መቼስ ይህቺ አመጽ የማያጣት ከተማ ተድበለቅልቃለች ብላ ትንግረኛለች ብዬ እየጠበቅኩ ነው…..በአልጋ ልብሱ ግማሽ እርቃኗን ቅጥ አልባ በሆነ ሁኔታ ለመሸፈን እየሞከረች ሞባይሏ ላይ አፍጥጣ ‹‹‹ቶሎ በል ልብስህን ልበስ…ፍጠን›› ‹‹ምን ተፈጠረ..…?ተረጋጊና ንገሪኝ እንጂ›› ‹‹አስር ሰዓት ሆኗል›› ‹‹እና›› ‹‹አስር ሰዓት ሆኗል እኮ ነው የምልህ…?›› ‹‹እና አስር ሰዓት ምን አለ…?››ምንም ሊገለጽልኝ አልቻለም ‹‹ከአራት ሰዓት በላይ እኮ ነው የተኛነው…ገና አንቦ እኮ ነው ያለኸው›› ‹‹.አረ ተረጋጊ …እኔ ደግሞ ምን ተፈጠረ ብዬ›› ‹‹ይቅርታ ..አጉል አደረግኩህ…በል ተነስ እንውጣ ››ብላ ልብሷን ለመልበስ ስትሞክር ጎተትኳትና ‹‹….ተመልሰሽ ተኚ››አልኳት ‹‹ለምን…?›› ‹‹ዛሬ አልሄድም…ልጄ አያቷ ጋር ነች ..ለአንድ ቀን ምንም አትሆንም…አብረን እናድርና ነገ ጥዋት እንለያያለን..አሁን እኔ ወጣ ብዬ አንድ ቦታ ደረስ እልና እመጣለው ..ሀያ ደቂቃ ቢወስድብኝ ነው… እሰከዛ ተኝተሸ ጠብቂኝ›› ‹‹አረ ተው አንተ ሰወ…አሁን ብትሄድ አትደርስም…?›› ‹‹እርግጥ ይመሻል እንጂ ደርሳለው..ግን መሄድ አልፈልግም…ዛሬ ጥዬሽ አልሄድም›› ‹‹አረ ባክህ… ዛሬ ጥለኸኝ ባትሄድ ነገ መሄድህ የት ይቀራል›› ‹‹ቢሆንም ማምሻም እድሜ ነው ሲባል አልሰማሽም›› እሷ እንደአልኳት ወደ መኝታዋ ተመለሰችና ተኛች ….እኔም ጫማዬን አጠለቅኩና ጉንጯን ስሜ ጥያት ወጣው.. . . . . ከሰላሳ ደቂቃ ቡኃላ ተመለስኩ ‹‹እንዴ !!!አሁንም ተኝተሻል…?›› ‹‹ትዕዛዝ ላክብር ብዬ ነዋ….እኛ ኢትዬጵያውያን የፖሊስ ትዕዛዝ በፍራቻ ነው የምናከብረው ..ይህን መቼስ አንተም ታውቃለህ …?›› ‹‹አረ አለውቅም… ምን ለማለት ፈልገሽ ነው.…?››.አልኳት….አልጋው ጠርዝ ላይ በመቀመጥ… ‹‹ያው ህጻን ሆነን ወላጆቻችን የሆነ ጥፋት እንዳናጠፋ ሲፈልጉ ወይም ስራ አናሰራ ብለን ስንረብሻቸው አደብ እንድንገዛ የሚያስፈራሩን ወይ በጅብ ነው ወይ በፖሊስ ነው›› ‹‹አንቺ ጅብና ፖሊስ አንድ ናቸው እያልሽ ነው….›› ‹አይ አልወጣኝም…እኔ ያልኩት ሁለቱም ማስፈራሪያዎች ናቸው ነው›› ‹‹ሙጢ ነገር ነሽ …ለማንኛውም ተነሺ ልብስ ልበሺና ወጣ እንበል…›› ‹‹እስከነተጠቀለለችበት አልጋ ልብስ አልጋውን ለቃ ወረደችና ልብሷ ወዳተቀመጠበት ወንበር አመራች… በመጀመሪያ ሱሪያዋን አነሳች ..ልትለብስ›› ‹‹አይ እሱን አትልበሺም››አልኳት ‹‹እና ምን ልልበስልህ……?ታጋች እኮ ነኝ ..በለበስኩት ልብስ ብቻ እንደጠለፍከኝ ዘነጋሀው እንዴ…?›› ‹‹አልዘነጋውትም….ግን ይሄንን ልበሺ ››ብዬ ይዤ የመጣውትን አረንጎዴ ፔስታል ከወለሉ ላይ አንስቼ ወረወርኩላት ..በአንድ እጇ ቀለበችውና ወንበሩ ላይ ቁጭ ብላ በመደነቅ ተሞልታ ከፈተችው…..ውስጡ ያለውን ነገር ጠረጵዛ ላይ ዘረገፈችው…በመጀመሪያ ያነሳችው ቀሚሱን ነው….ባለ ሰማያው ቀለም ረጂም የእራት ቀሚስ ….በፍዘት አፎን ከፈታ ምንም ሳትናገር ዝም ብላ ለበሰችው…...ከዛ ከገዛውላት ግማሽ ደርዘን ፓንቶች መካከል አንዱን አነሳችና ፊት ለፊቴ ቆማ አጠለቀች…. በስተመጨረሻ ጫማውን አደረገች…... ተስተካክላ ፊት ለፊቴ ቆመች..
በወንድነት እና በሴትነት መካከል የሚዋልል የነበረው አቋምና ባሀሪዋን ወደሴትነት እንዲህ
በግድም ቢኆን ስትሳብ ውበቷ በእጥፍ ጎላብኝ….
‹‹አረ በስመአብ…ይሄንን ሁሉ ውበት የት ደብቀሽው ነበር………?››
የእኔን ሙገሳ ችላ ብላ‹‹አንድ ሚስጥር ልንገርህ……?››
‹‹ንገሪኝ››
‹‹ማንም ወንድ እንዲህ አይነተ ስጦታ ገዝቶልኝ አያውቅም››
‹‹ይህንን ስለነገርሺኝ ደስ ብሎኛል››
‹‹ሌላም የምነግርህ አለኝ››
‹‹እየሰማው ነው››
‹‹ነፍስ ካወቅኩ ጊዜ አንስቶ ቀሚስ ለብሼ አላውቅም…ምንም ቀሚስ የለኝም….አውነቴን
ነው….አሁን ቀሚሱን ለብሼ ፊትህ ስቆም የተለየ ስሜት ነው የተሰማኝ›››
‹‹የተለየ ስሜት ስትይ..……?የደስታ ››
‹‹አይ እንደዛ ብቻ አይደለም …የሆነ የመረጋጋት…የመቀዝቀዝ….የመሽኮርመም…እኔ እንጃ
መግልፅ አልቻልኩም..ግን በጣም አመሰግናለው፡፡››
‹‹ግድ የለም ምስጋናው ይቆየኝና አሁን ወጣ እንበል….››
‹‹እሺ› አለችና ቀድማኝ ወደ በራፍ እርምጃዋን ቀጠለች…
‹‹እንዴ !!!ወዴት ነው……?››
‹‹እንሂድ አላልከኝም እንዴ..……?››
‹‹አንድ ሴት እኮ እንሂድ ከተባለች ቡኃላ ለመዘጋጀት በጣም ፈጣን ከኆነች አንድ
ሰዓት..ከልሆነም ሁለትን ሶስት ሰዓት ይፈጅባታል..››
‹‹አልገባኝም..ምን ልትሆንበት……?››
‹‹ስትጠጣጠብ..ስትቀባባ..ስትኳኳል ..ልብስ ስትለካ ስታወልቅ….መስታወት ፊት ቆማ
አለባበሷን ስታስተካክል ..››
‹‹ቀልደኛ ነህ…ልኳኳል ብልስ ምኔን እኳኳላለው………?ለዛውስ ያለመደብኝን….ጋሼ ዜና
ምን ይሉኛል መሰለህ ..ሴት ሁኚ…ሁሌ ምክራቸው ሴት ሁኚ ነበር››
‹‹ማናቸው ጋሽ ዜና .. ……?››
ጋሽ ዜና እንደአያቴ የማያቸው ከጎረቤታችን የሚኖሩ ከውልደቴ እስከዛሬ የሚያውቁኝ
እንደአያቴ የማያቸው ሙሁር ግን ደግሞ ደሀ …(ለካ እዚህ አገር ምሁርነት እና ድህነት
አብረው የሚሄዱ ዘማዳሞች ናቸው) አዛውንት ናቸው፡፡››
‹‹እና ሴት ሁኚ ሲሉሽ..አረ ሴት ነኝ ብለሽ ቢያንስ ስንጥቁን በፎቶም ቢሆን አንስተሸ
ማረጋገጫውን አታሳያቸውም››
‹‹እሷቸው እኮ እንደላንጠለጠልኩና ስንጥቅ መሆኔን በደንብ ያውቃሉ..ለማለት የፈለጉት
ሴት ሆነሽ ተፈጥረሻል እና የሴትን ተፈጥሮዊ ባህሪ ተላበሺ ማለታቸው ነው….ሴቶቸ ወበት
አድናቂ ናቸው..ሴቶች ሰላም ወዳዶች ናቸው…ሴቶች የፍቅር ዘማሪዎች ናቸው….ሴቶች
ልስልስ ናቸው..ሴቶች ለተፈጥሮ ቅርብ ናቸው..ሊዩክሌር ቦንብ ለመስራት በላባላቶሪ
ከመዳከር በግቢያቸው ውስጥ ያለ አበባ ውሀ እያጠጡ እና እየኮተኳቱ ማሳደግና በዛ
መደመምን ይመርጣሉ….ሴቶች ቀለል ያለ ያልተወሳሰበ ኑሮን ይመርጣሉ..ሴቶች ስሜተ
ሙሉ ናቸው…ሴቶች እናቶች ናቸው..እናትነት ደግሞ የፍቅር መህደር ማለት ነው….እና ሴት
ሁኚ ሲሉኝ ምን ለማለት ፈልገው እንደሆነ ይገባኛል….ድብድብና አንባጎሮውን ቀንሺ ሊሉኝ
ፈልገው ነው….ዘረፋውንና ማጅራት መምታቱን ባንቺ አያምርብሽም ሊሉኝ ነው…››
‹‹ባይገባኝም ገብቶኛል..በይ አሁን እንሂድ..አልኩና ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ቤርጎውን
ቀለፍንና እጅ ለእጅ ተያዘን ግቢውን ለቀን ወጣን….የሙዚቃ ሁካታ ማያደነቁርበት ቤት
ፈልገን እራታችን ልንበላ
..
..
ሁለት ሰዓት ሲሆን እራታችንን በልተን በማጠናቀቅ ከወደ መጠጡ እየወሳሰድን ጫወታችን
ቀጥለን ነበር..የጫወታው ርዕስ ወደ ሮማን ዞሯል… ወደ አሳዳጊ እናቷ
‹‹ቆይ እናትሽን እሷ እንደገደለቻት በምን አወቅሽ….……?እንደነገርሺኝ በወቅቱ አንቺ ልጅ
ነበርሽ……?››
‹‹አዎ ልጅ ነበርኩ..ያወቅኩት በቅርቡ ነው ..የዛሬ ስምንት ወር አካባቢ››
‹‹እንዴት ልታውቂ ቻልሽ››
‹‹በአጋጣሚ……ምን መሰለህ....እናቴ ስትሞት ለአንድ ሳምንት ታማ ነበር…በዛ
በታመመችበት ሰዓት ከስሯ ኩርምት ብዬ አይን አይኗን ሳይ ነበር የምውለው…እና ትዝ
ይለኛል በመጨረሻዋ ቀን ከመሞቷ ከአንድ ወይም ከሁለት ሰዓት በፊት እሮማን ፍቱን
የባሀል መድሀኒት ነው በሽታሽን ነቅሎ ያወጣልሻል አለቻትና አንድ መድሀኒት በብልቃጥ
አምጥታ አጋተቻት….ብልቃጧ የመድሀኒቱ ቀለም እና ሽታው ምን ጊዜም ከአዕምሮዬ
አይጠፋም…የመድሀኒቱ ቀለም ዝልግልግ አረንጎዴ ሳር መሰል ሲሆን ሽታው ግን እንደዚህ
ነው ብዬ መናገር ማልችለው በህይወቴ ወደ አፍንጫዬ ገባቶ የማያውቅ የተለየ ሽታ
ነው…..እናቴን ግን ሊያድናት አልቻለም..ሁል ጊዜ እናቴ ስትናፍቀኝ ወደ አይምሮዬ
የሚመጣው አልጋ ላይ የተዘረረ የእናቴ በበሽታ የደከመ ሰውነት..አረንጓዴ የተዝለገለገ
ፈሳሽ..ከፈሳሹ የሚበተነው ሽታ..ግርም ነው የሚለኝ..እንዚህ ነገሮችን ለምን ደጋግሜ
እንደማስታውስ ለራሴም ግራ ግብት ይለኝ ነበር…..
‹‹እና ከዛሬ 8 ወር በፊት አንድ ስራ ለመስራት ፈለግኩ››
‹‹ምን አይነት ስራ ?››
‹‹አንድ በጣም የሚያስጠላኝ አራጣ አበዳሪ ሰውዬ ነበር…በህይወቴ ከማውቃቸው ሰዎች
ሁሉ የመጀመሪያው ወንበዴ እና ጨካኝ ሰው ነው….አንድ ቀን ወደ ቤቱ ወሰደኝ..ይገርምሀል
ሚኖርበት ቢላ 13 ክፍሎች ያሉት የተንቆጠቆጠ ነው…፡፡ያን የሚገርም ቤት የገነባው
ጠቅላላ ሀብቱንም ያከማቸው በተዘረፈ ብር ነው..››
‹‹ሚስት የለውም እንዴ ?››
‹‹አለው 32 ዓመት አብራው የኖረች ሚስት አለው…ልብ በሽተኛ ሆና ለህክምና ልጇቾ ወደ
ውጭ ስለወሰዷት ለብቻው ነው የሚኖረው…..የልጅ ልጅ ያየ የስልሳ ወይም የሰባ አመት
ሽማጊሌ እኮ ነው….መጀመሪያ አንድ ሺ ብር ከፈለኝና ይዞኝ ሄደ….መኝታ ቤት ከገባን ቡኃላ
ልክ እንደ ሀያ አመት ጎረምሳ ፊልም ከፈተ..››
‹‹የምን ፊልም… ?››
‹‹የወሲብ ፊልም ነዋ…ፈረንጆች የሚጨመላለቁበትን ፊልም….ልብሱን አወላለቀ እና ያንን
ቀፈታም እንደከበሮ የተነረተ ሆዱኑ አንዘርጥጧ ፊቴ ቆመ..››
‹‹ሰውዬ ተኛ እንጂ››አልኩት
‹‹ተይ እንጂ ቆንጂት ..ምን አስተኛን…እድሜችን ሙሉ ተኝተን ስናረግ ነው የቆየነው…አሁን
በፊልሙ እንደምታያቸው ዘመናዬቹ ነው ማድረግ የምፈልገው…ያኛውማ አይነት ሰልችቶኛል
…ካአሁን ቡኃላ ጸኝጾ ማድድግ ለማለድ ብቻ ና የሚጠቅመው..እኔ ደግሞ አንቺ
እንድታስደስቺኝ እንጂ እንድትወልጂልኝ አልፈልግም››ብሎ ገለፈጠ…በሱ ቤት መቀለድ ነው
‹‹እሱ ይወደድብሀል››አልኩት….
ወደ ኮመዲኖ ሄደና መሳቢያውን ሳበው..ይገርምሀል ኮመዲኖው ሙሉ በገንዘብ የተሞላ
ነው…የተሰረ የታሰረ ብር..አንዱን መዥርጦ አመጣና እጄ ላይ አስቀመጠልኝ››
‹‹እንዴት ነው የምትፈልገው ?››
‹‹እንድትጠቢልኝ››
‹‹ምን ? ››
‹‹አዎ እንደዛ ነው የምፈልገው..አየሻቸው አይደል ፊልሙ ላይ ያሉትን ቆነጃጅቶች..እንዴት
እንዴት የሰውዬውን ነፍስያ እንደሚያስደስቱለት››
‹‹ግን እኮ እንትኖት ልፍስፍስ እንዳለ ነው..ካልቆመ እንደዛ ለማድረግ ያስጠላል…››
‹‹አቁሚዋ…. ስራሽ ማቆም አይደል… ?››
‹‹አይደለም ጌታዬ …ስራዬ የቆመውን አባብሎ ማስተኛት ነው ››
‹‹እኔ እኮ አስር እጥፍ የከፈልኩሽ..የተኛውን ቀስቅስሽ በማቆም ..እንዳልሽው ከእንደገና
አባብለሽ እንድታስተኚው ነው…››
‹‹ከዛ እንዴት ሆናችሁ ?››የምታወራለልኝ ወሬ እበሳጨኝም እናደደኝም..በምትለው ሽማግሌ
ልናደድ ወይስ በእሷ በራሷ መለየት አቃተኝ፡ነው ወይስ እየቀናው ነው ?፡፡
‹‹ከዛማ እንዲሁ ሲንበዛበዙብኝ አደሩ…እንትናቸው እንኳን በእኔ ሀይል በቢያግራምም
ሚቆም አይነት አልነበረም ለማንኛውም ነጋና ተለያየን…››
በሳምንቱ ያገናኘኝን ደላላ ላኩት
‹‹ለምን ?››
‹‹ ለመድገም ነዋ..እኔ ደግሞ እንኳን እንደሳቸው አይነት በዝባዛ ሽማግሌ ይቅርና እንደአንተ
አይነት መለሎ ወንድ ቢሆንም መድገም ብሎ ነገር ነው የሚያስጠላኝ…ግን እዛ ኮመዲው
ውስጥ ታጭቆ ያየውት ብር አሻፍዶኝ ስለነበረ..እምቢ ማለት አልቻልኩም…››
‹‹ድጋሚ ልትጠቢ ?››ሳላስብ የጠየቅኩት አስቂኝ ጥያቄ ነው
‹‹አይ እንትናቸውን ሳይሆን ብራቸውን ልጠባ…እና ሮማንን አማከርኳት…..እንዳጋጣሚ
ቤተሰብ ልጠይቅ ብላ ከአዲስ አበባ ውጭ ነበረች..እና በስልክ ነው ያማከርኳት…እና
የሚያደነዝዝ መድሀኒት እንድትሰጠኝ ጠየቅኳት….ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ስራ ስሰራ
የምጠቀመውን መድሀኒት የምትሰጠኝ እሷው ስለነበረች…የተለመደ ጥያቄ ነበር የጠየቅኳት
የት እንደሚገኝ በምልክት ነገረቺኝ..ከነተቀመጠበት የእቃ አይነት …ቁልፍን ካለቺኝ ቦታ
አገኘው..መኝታ ቤቷ ጋባው… ቁም ሳጥኗን ከፈትኩ ..በሌላ ቁልፍ ቁም ሳጥኑ ውስጥ
ያለውን አንድ አነስታኛ ሌላ ሳጥን ከፈትኩ..ኣዛ ሳጥን ውስጥም ሌላ የተቆለፈች ሳንቲም
ማጠራቀሚያ የምታህል የብረት ሳጥን አለች …ተቆልፋለች …ቁልፉ የለኝም..ደወልኩላት
‹‹ ሳጥኑን በምን ልክፈታት ?››
‹‹ቁልፍን ይዤ ነው የመጣውት …ገንጥያት..አደራ ቀስ ብለሽ..ውስጥ ያሉት መዳኒቶቹ
በጣም አስፈላጊ ናቸው… እንዳትሰባብሪብኝ እና እንዳይደፈ››
‹‹እሺ ››በማለት ስልኳን ዘጋውና በጥንቃቄ ገነጠልኩት..እንኳን ያቺን የምታክል ሚጢጢዬ
ቁልፍ ይቅርና ሌላውም ቢሆን ቁልፍ መገንጠል የተካንኩበት ሞያዬ ነው፡፡
ስገነጥለው አምስት የሚሆኑ የተለያየ መጠን ያላቸው ብልቃጦች አገኘው…ነጭ ብልቃጥ
ውስጥ ያለው ነው ያለቺኝ..ነጭ ብልቃጥ ደግሞ አንድ ብቻ ነው ..ፈገግ ብዬ አነሳውትና
መልሼ ልከድነው ስል የሆነ ነገር ገፋፋኝና ከጎኑ ያለውን ሌላውን ብልቃጥ አነሳውት..የሆነ
በጣም የማውቀው ብልቃጥ መስሎ ተሰማኝ …በዝግታ ከፈትኩት…አፍንጫዬ በሆነ ሽታ
ተሞላ ….በህይወቴ ይሄንን አይነት ሽታ ለሁለተኛ ጊዜ መማጌ ነው…ወደ መሬት ትንሽ
አፈሰስኩለት ይበልጥ ለማረጋገጥ …የተዝለገለገ አረንጓዴ ፈሳሽ..እናቴን የጋተቻት ላካ
መድሀኒት ሳይሆን ሞት ነበር…እናቴን ለካ በሽታው ሳይሆን በዚያች አረመኔ የተሰጣት መርዙ
ነበር የገደላት….እርግጥ በጣም ጨካኝና አረመኔ እንደሆነች አውቃለው..ዘራፊና ገዳይ
እንደሆነችም የአይን ምስክር ነኝ…..እኔም እራሴ የእሷ ውጤት ነኝ…ግን የገዛ እናቴን
ገድላታለች ብዬ ለደቂቃ እንኳን ተጠራጥሬያት አላውቅም ነበር….እና እንደእብድ
አደረገኝ..ያንን መርዝ በወቅቱ ተግቼ እናቴ የሞተችውን ሞት ለመሞት ተመኘው….ሰውዬውን
ለመዝረፍ የነበረኝን ሀሳብ ተውኩት… ብልቃጡን ኪሴ ከትቼ ጥዬ ወጣው.
.ለካ ያንን ሁሉ ዘመን ስታሾፍብኝ ነበር…ለካ እናቴን ገድላ በእኔ ስትበልፅግ ነበር…..ለካ
ሸርሙጣ ያደረገቺኝ በዕቅድ ነበር..ለካ ስዘርፍ የኖርኩት ለእሷ ነበር…ሁሉ ነገር ግልጽልጽ
አለልኝ..ያንቻው ነው እያለወች በስሞ ስትገዛ ከኖረችው ንብረት አንዲቶንም
እንደማታቀምሰኝ እርግጠኛ ሆንኩ…እግዚያብሄር ባያጋልጣት.. ተጠቅማብኝ ተጠቅማብኝ
የጠገበቺኝ ጊዜ ለዛውም በቅርብ እኔንም በዚያ መርዝ ልታስወግደኝ እንደምትችል እርግጠኛ
ሆንኩ..ከዛን ቀን ጀምሮ እሷንም ሌብነት የሚባለውንም ነገር እርግፍ አድርጌ
ተውኩ…..ሁለቱንም ዞር ብዬ ላላያቸው ለራሴ ማልኩ፡፡
‹‹እሷስ አልፈለገችሽም ?››
እሷማ የነዳጅ ጉድጓድ እንደደረቀበት አረብ ነው ያዘነችው..ከእኔ ለመታረቅ እና ወደ ቤት
እንደምለስ ያላደረግችው ጥረት ያለመነችው ልመና አልነበረም…››
‹‹እና ተስፋ ቆርታ ተወችሽ ?››
‹‹እስከአሁን እንግዲህ እየተጠባበቅን እንኖራለን…እርግጠኛ ነኝ የሆነ ሆነ ቀን እንደማጠቃት
ትጠረጥራለች… ስለዚህ በተጠንቀቅ እና በመበርገግ ነው የምትኖረው..እኔም እንደዛው
ከፍራቻዋ የተነሳ ጥላዋንም የማታምን ሰው ስለሆነች የሆነ ነገረ ልታደርገኝ እንደምትችል
ስለማውቅ እንደሸከከኝ ነው.... የምኖረው ማን እንደሚቀድም እስከአሁን አለየም ››
‹‹በጣም ይገርማል…››
‹‹አዎ ይገርማል››
‹‹ስልኬ ጮኸ››
‹‹ከሻምቡ ነው..የእህቴ ልጅ ነች የደወለችው›
‹‹ሄሎ አጎቴ››
‹‹ሄሎ በሻዱ…ሰላም ነሽ ?››
‹‹ሰላም ነኝ….ነገ ትመጣለህ እንዴ ?››
‹‹አዎ መጣለው ..ምነው ?›
‹‹አይ ምንም አይደል.. ?እንዲሁ ነው የጠየቅኩህ እናንተ ቤት ነኝ››
‹‹መጣሽ እንዴ… ?››.
‹‹አዎ …አኩዬ ስትደውልልን እማዬ ሂጂላቸው አለቺኝ››
‹‹እና ሚጡ አስቸገረቺሽ ?››
‹‹አረ አላስቸገረቺኝም ..አሁን ተኝታለች››
‹‹አይ ጥሩ ነው..እማዬስ ?››
‹‹እሷም ተኝታለች››
‹‹በቃ ነገ አስከ ስድስት ሰዓት እደርሳለው…አሁን አንቺም ተኚ ደህና እደሪ››
‹‹አሺ ደህና እደር አጎቴ››ስልኩን ዘጋው፡፡
‹‹የእህቴ ልጅ እቤት መጥታ ነው..››
‹‹ገባኝ…አሁን ስትሄድ ምንድነው የምታደርገው ?››
‹‹ማለት.. ?›
‹‹ልጅህን ማነው የሚጠብቅልህ ?››
‹‹ሰራተኛ እፈልጋለዋ››
‹‹ታገኛለህ ?››
‹‹የግድ ማግኘት አለብኝ..ዘመድ አዝማድ ሁሉ ተሯሩጠው ያገኙልኛል ብዬ አስባለው››
‹‹አይ ጥሩ ነው…››
እንግዲያው እኔም ወደ ሸገሬ ገብቼ ሶስት ቀን ሙሉ ወቋረጥኩተ ስራዬ ልመለስ….››
‹‹ስራዬ..የምን ስራ ?››ጥያቄው የእውነቴን ነበር…ስራዋ ምን ነበር…ምን ስትሰራ ነው
የተገናኘነው… ?ከአዕምሮ ተሰርዞል
‹‹የምን ስራ ትላለህ እንዴ.. ?ምን ስሰራ ነው ያገኘኸኝ ….ሽርሙጥና ነዋ››
‹‹ሽርሙጥና››
‹‹አዎ ሽርሙጥና››
‹‹በፍፅም ወደዛ ህይወት አትመለሺም..ሽርሙጥናውንም እንደስርቆቱ እርግፍ አድርገሽ
መተው አለብሽ….››
‹‹እየቀለድክ መሆን አለበት››
‹‹እየቀለድኩ አይደለም..እኔ በህይወት እያለው አንቺ ዳግመኛ ወደ እዛ ሕይወት
አትመለሺም››
‹‹እና ታዲያ ምን ልሁን ?››
‹‹ምን ሁኚ ልበላት…ሌላ ምን ስሪ ልበላት….ድንግርግሬ ወጣ..በዚህ ጊዜ የእሷ ስልክ
ጠራ..አነሳችው
‹‹ሄሎ እሱባለው››
ማነው እሱ ባለው ? በአዕምሮዬ የመጣብኝ ጥያቄ ነው…‹‹ሄሎ እሱባለው››
‹‹አለሽ እንዴ ጂጂ….?››
‹‹አለውልህ››
‹‹ጥዋት ላገኝሽ ፈልጌ ነበር››
‹‹ትንሽ ራቅ ብያለው…ነገ ከሰዓት እንገናኝ….?››
‹‹ይቻላል››
‹‹ ግን ችግር የለም አይደል….?››
ንግግሯን ሳትጨርስ እና ለጥያቄዋ መልስ ሳታገኝ ስልኩ ተቋረጠ‹‹…ምን አይነት ቁሺም
ነኝ… ቻርጅ ሳላደርግ ውዬ አሁን ስልኬ ተዘጋብኝ››
‹‹በእኔ ደውይአ››ብዬ አቀበልኳት
‹‹አይ ስልኩን በቃሌ አላቀውም..እንግባና ቻርጅ አድርጌ ደውልለታለው››አለቺኝ ..በውስጤ
ቅሬታ እየተሰማኝ እንዳለችኝ ሂሳብን ከፍዬ አስነሳዋትና አንድን እጄን ትከሻዋ ላይ ሌላውን
ደግሞ በወገቧ ዙሬያ ጠምጥሜ ይዤት ወጣው…
እንደደረስንና ቤርጎቸንን ከፍተን እንደገባን ሁለታችንም ወደ አልጋው ነው የሮጥነው…
አልጋው ላይ ከሰፈርኩ ቡኃላ ልብሴን ማውለቅ ስጀምር..እሷ በተቃራኒው ቀሚሱን
ሳታወልቅ ከውስጥ ጂንስ ሱሪዋን አደረገች
‹‹ሰው ሊተኛ ሲል ልብሱን ያወልቃል አንቺ በተቃራኒው ታደርጊያለሽ..….?››
‹‹መቼም ሁለታችንም አውልቀን አንተኛም››
‹‹ብንተኛ ምን አለበት….?››
‹‹ነገር አለበት››
‹‹የምን ነገር….?
‹‹ትልልቅ ሰዎች ሚያደርጉት ነገር..››
‹‹እየቀለድኩ እኮ አይደለም..ልብስሽን አውልቀሽ ብተኚ ደስ ይለኝ ነበር››ቅሬት ባጋተ
የሚርገበገብ ድምጽ
‹‹ምንም አልገባህም እንዴ….?››አለቺኝ ሱሪዋን አጥልቃ ከጨረሰች ቡኃላ ቀሚሷን በአንገቷ
በኩል ሞሽልቃ እያወለቀች
‹‹ምኑ ነው ያልገባኝ….?››
‹‹በጣም እኮ ነው የወደድኩህ..እርግጥ እንዲህ ስል ውስጤን ንዴትና ብስጭት እየወረረኝ
ነው..ቢሆንም ግን ወድጄሀለው…ያ ደግሞ በእኔ ህይወት ትልቅ ነገር ነው ….አዲስ እና
ያልተለመደ ነገር…ስለዚህ ላበላሸው አልፈልግም..እስኪ ጥቂትም ቢሆን ከወንዶችም
መካከል ጥሩዋች አሉ ብዬ እንዳምንና እንዳወራ እርዳኝ››አለቺኝ ከላይ ቲሸርቷን ለብሳ አልጋ
ላይ እየወጣች….እኔም አወላልቄ ጨርሼ በፓንት እና በፓካውት ብቻ ነበርኩና እንደእሷ
አደረግኩ
‹‹አወሳሰብሺብኝ እኮ …. ››
‹‹ባክህ ለራሴም ተወሳስቦብኝ ነው ››
‹‹ቆይ ለአንቺ ወንዶች ሁሉ መጥፎዎች ሆነው ነው የሚታዩሽ….?››
‹‹አይ የሚታዩኝ ሳይሆን በርግጠኝነትም መጥፎዎችና የማረቡ እብሪተኞች ናቸው…እኔ ከጋሽ
ዜና በስተቀር ጥሩ የሚባል ወንድ አላጋጠመኝም..ያው እሷቸውም ምን አልባት አዛውንት
ስለሆኑ ሊሆን ይችላል…በጣም የተማሩ እና አንባቢም ስለሆኑ ሊሆኑ ይችላል …..አዎ
እሳቸው አስተሳሰባቸውም አኗኗራቸውም ሁለ ነገራቸውም ከብዙሀኑ ወንዶች ፍጽም የተለየ
ነው…
‹‹እኔስ…..….?››የምላስ ወለምታ ..አዳልጦኝ የጠየቅኩት ጥያቄ ነው፡፡
‹‹አንተ… እኔ እንጃ …ያንተ ሚዛን የተለየ ነው….ምን አንተ ላይ እንዳየው አላውቅም…….?
ምን አልባት ፍቅር ሲይዝህ በዛ ሰው በጣም ስትሳብና ግን ደግሞ መኑ እንዳማረከገህ
አይገባህም ይሁናል ….? ..ግን ደግሞ አብረኸው መሆን ትራባለህ…. በእቅፉ ውስጥ
መጥፋት ያጓጓሀል….በትንፋሹ መቅለጥ ያምርሀል …ወይም ጭው ያለ በረሀ ውስጥም
ቢሆን ከእሱ ጋር ብቻህን መኖርን ህልምህ ይሆናል….እሱን ስለማጣት ስታስብ ውስጥህ
በሽብር መናጥ ይጀምራል..አዎ ፍቅር የሚሉት የሰው ልጅ ጣጣ እንደዛ አይነቱ ነው
መሰለኝ››
‹‹የሚገርም አገላለጽ ነው….እና አሁን በገለጽሺው መጠን አፍቅረሺኛል ማለት ነው….?››
ደነገጠች‹‹ማ….? እኔ …….?ማንን….?››
‹‹እኔን ነዋ..››ቆፍጠን ብዬ
‹‹እንዴት ሊሆን ይችላል..….?ከተዋወቅን እኮ ገና ሶስተኛ ቀናችን ነው…..በሶስት ቀን
በፍቅር መያዝ አለ እንዴ…….?››
‹‹በፍቅር ለመያዝ ግን ስንት ቀን ያስፈልገል….? ….በሰከንድ ሽራፊም ሊሆን ይችላል እኮ…
እኔ ግን አፍቅሬሻለው…በጣም ነው የወደድኩሽ..ይሄንን ቃል ከሞች ሚስቴ ውጭ ለማንም
ሴት ተጠቅሜው አላውቅም…በጣም ነው ያፈቀርኩሽ…ስላፈቀርኩሽም ደስተኛ ነኝ››ወሬያችን
ሁለታችም ከጭንቅላታችን ቀና በማለት ትራሳችንን በመንተራስ ፊት ለፊት እየተያየን ነው
‹‹አይ እንዳልከው ከሆነ … ፍቅር ሳይሆን መጋኛ ነክቶሀል ..አየህ መጋኝ ድንገት ነው ለሊት
በራፍ ከፍተህ ስትወጣ..ወይንም ተዘግቶ የቆየ ቤት ድንገት ከፍተህ ስትገባ ..አዎ ያዝን
ጊዜ በጋኛ ድንገት አጠናገረው ይባለል…እና ፍቅርም እንደዛ ከሆነ ፍቅር ሳይን እርግማን ነው
በለው….እንዲህ ማረፊያውን እንኳን የማያውቅ….?››
‹‹ምን ማለት ነው..….?››
‹‹እሺ አፈቀርከኝ…ምን ልታደርገኝ ነው..ሰው እንዴት አንድ ሸርሙጣ ያፈቅራል….?››
‹‹እኔ ሸርሙጣ አላፈቀርኩም ..እኔ ያፈቀርኩት አንቺን ነው..አንቺ ደግሞ ሰው
ነሽ….ሰው….እጅጋየው የምትባለዋን ቆንጆ ብሩህ አዕምሮ ያላትን የሚደንቅ የህይወት ታሪክ
ባለቤት የሆነችውን ከአልማዝ የጠነከረች ልጅን እንዳፈቀርኩ ነው የማውቀው..በዛም
በጣም ዕድለኛ እንደሆንኩ ነው የሚሰማኝ..››
በጭቃ ተለውሶ አደባባይ ላይ የተጣለን ወርቅ ወርቅነቱን አውቆ በማንሳት ጭቃውን አጽድቶ
ለመጠቀም እድልና ብልሀትን ይጠየቃል፡፡አኔ ብልህ ነኝ ብዬ ባላስብም እድለኛ ግን
እንደሆንኩ እርግጠኛ ነኝ፡፡››
‹‹ጥሩ ነው..ማፍቀር መፍትህ ነው..እኔ ግን ነገ የምለየውን ….መቼም ደግሜ የማላገኘውን
ሰው አፍቅሬዋለው ብዬ መጃጃል አልፈልግም..አዎ አልፈልግም……በፍፅም..አዎ አንተን
ማፍቀርማ የለብኝም››ለእኔ የምታወራ ሳይሆን ከራሷ ውስጠት ጋር ሙግት የገጠመች ነው
የሚመስለው፡፡
‹‹ለምን አንሄድም….?››
‹‹ወደ የት….?››
‹‹ወደ ሻንብ››
‹‹ምን ለማድረግ..….?››..
‹‹በቃ አብረን እንኖራለን..ሻንቡ ታያታለሽ..እርግጥ ካደግሺባት አዲስ አበባ ጋር ስትነጻፀር
ቀበሌ ልትሆንብሽ እና ሊደብርሽ ይችላል … ቢሆንም ልጄን ትተዋወቂያታለሽ..እሷን
በእርግጠኝነት በጣም ነው የምትወጂያት….እናቴም የምትወድሽ ይመስለኛል››
‹‹የእውነትህን ነው….?››
ለእሷ ሳይሆን ለእናንተ እወነቱን ልንገራችሁ የማወራው ነገር ሁሉ የእውነቴን ይሁን ወይስ
የሆነ ቅዣት ውስጥ ሆኜ የምዘባርቀው እርግጠኛ አይደለሁም….ይህቺ ልጅ አዕምሮዬን
እንዲሰለብ እና የማገናዘብ ኃይሌ እንዲሞጠጥ አደረገች እንዴ….?
‹‹እውነቴን ነው..በቃ አብረን እንሂድ ..ታይውና ከደበረሽ ትመለሺያለሽ››
‹‹ካልደበረኝስ…….?ሁሉ ነገር ቢመቸኝስ….….?››
‹‹እሱ አይደል የሚፈለገው..››
‹‹ምንህ አድርገህ ታኖረኛለህ….?››
‹‹ብታገቢኝ ደስ ይለኛል››
‹‹አረ …አንተ ሰው ጤነኛ አትመስለኝም..ነገ የምትፀፀትበትን ነገር ዛሬ አትዘባርቅ..ነው
ወይስ ሰከርክ….?››
‹‹እንዳልሰከርኩ አንቺም ታውቂያለሽ..እሺ ብለሺኝ ካገበሽ በእውነቱ በጣም እድለኛ ሰው
እንደሆንኩነው እራሴን የምቆጥረው…በእወነት አንቺን አጠገቤ እንድትኖሪ የማላደርገው ነገር
የለም..ምን አልባት እቤት መዋል ይደብረኛል የምትይ ከሆነ የሆነ ሱቅ ነገር ከፍትልሻለው…
በቃ ኮስሞቲክ ቤት..ወይንም ቡቲክ…የፈለግሽውን….››
‹‹አላምንህም››አለቺኝ ፍርጥም ብላ..እውነቶን ነው..ለወንዶች መራር ጥላቻና ከልክ ያለፈ
ንቀት ያላት ልጅ እንዲህ መሰሉን የእን ቅዣት እንደውም አመንኩህ ብትል ነበር
የሚገርመው…
‹‹አላምንህም.. ነገውኑ ማለት ጥዋት እዚሁ ደብተሬ ላይ ሀምሳ ሺ ብር አለ… ባንቺ ስም
አዞርልሻለው..አዛ ስንደርስና ስራ...ስትጀምሪ ደግሞ የተወሰነ ተጨማሪ
ጨምርልሻለው..አይዞሽ ልጅ ጠባቂ ያደርገህኛል ብለሽ ሰግተሸ ከሆነ እሷዋን የምትንከባከብ
ልጅ እንደማገኝ ማረጋገጫ ሰጥሻለው..››
‹‹አመረርክ እንዴ ሰውዬ ….?እኔ እንደውም አሁን ካልከኝ ሁሉ ያጓጓኝ ልጅህን መንከባከብ
እና እንደእናቷ ጉያዬ ውስጥ ሸጉጬያት ስታለቅስ ላባብላት እና እሹሩሩ እያልኩ ላስተኛት
ብችል ብዬ ነው…››
‹‹እና አድርጊዋ ..እናቷ ሁኚ…….. ››
‹‹በምንም አይነት መንገድ…….?ላገባህ እንደሆነ አልችልም..››
‹‹እሺ አታግቢኝ …ግን አብረን እንሂድ እና ሌላ ስራ ጀምሪ ….ቢያንስ እንደወንድምሽ
ቁጠሪኝና በቃ ባለውበት አካባቢ ኑሪ …ጥሩ ጓደኛሞች እንሆናለን..በፈጠረሽ ወደ እዛ ከተማ
አትመለሺ….ባይሆን በቅርብ ወደ ነቀምት ቅያሬ ጠይቃለው..ነቀምት ትልቅ ከተማ ስለሆነ
እዛ አይደብርሽም››
‹‹እኔ ሚስትህም እህትህም መሆን አልፈልግም››
‹‹አረ በፈጠረሽ››
‹‹ሰራተኛህ አድርገህ ቅጠረኝ››
‹‹ምን….?››
‹‹አዎ የልጅህ ሞግዚት አድርገህ ቅጠረኝ….ሚስትም መሆን ነጋዴም መሆን አልፈልግም››
‹‹እኔ አንቺን ሰራተኛ አድርጌ.….?.››
‹‹አዎ..ለሄደችው ሰራተኛህ ስንት ነበር የምትከፍላት….?››
‹‹በወር ሁለት መቶ ብር››
‹‹ለእኔ ሶስት መቶ ብር አድርግልኝ…››
‹‹እየቀለድኩ እኮ አይደለም….?››አልኮት ሹፈት አዘል በሚመስለው ንግግሯ ተበሳጭቼ…
‹‹እኔም ቀልዴን አይደለም..ነው ወይስ እድሜዬን በሙሉ በሽርሙጥና እና በስርቆት
ስላሳለፍኩ የሞያ ነገር ኔፓ ነች ብለህ አሰብክ….በሞያ አትጠራጠር…አድሜ ለዛች ጭራቅ
ሮማን ተብዬ ….እጄን በማማሲያ እየቀጠቀጠች ነው ሞያ ያስተማረችኝ››
ምመልስላትን አጣውና ዝም አልኩ….በዚህ መካከል እሷ ተነሳችና ተንጠራርታ ስልኳን
ከተሰካበት ነቀለችና ከፈተችው ….ደወለች
‹‹ሄሎ እሱባለው››
ጆሮዬን ቀስሬ ማዳመጥ ጀመርኩ……
‹‹ሄሎ ጂጂ..ስሞክርልሽ እኮ እንቢ አለኝ››
‹‹አዎ ስልኬ ቻርጅ ጨርሶ ነበር…››
‹‹እንደዛ እንደሆነ ገምቼ ነበር..››
‹‹አዎ….ምነው ግን ችግር የለም አይደል….?››
‹‹አረ ፒስ ነው… ዛሬ እሁድ አይደል..የዕቁብ ቀን እኮ ነው››
‹‹እና ጎደለብህ እንዴ….?..››
‹‹አረ አልጎደለብኝም..አስር ሺ ብር ጥዬ እንደውም አንድ ሺ ሶስት መቶ ብር ግልባጭ አለ››
‹‹አይ ጥሩ ነው….ግልባጩ አንተ ጋር ይቆይ..ስፈልገው ደውልልሀለው››
‹‹አይ ለዛ አይደለም የፈለግኩሽ..ዕቁቡ ወጥቶልሻል››
‹‹ወጣ ..››
‹‹አዎ ወጥቶልሻል…ግን አልተቀበልኩትም….አሁን የደውልኩት ጥዋት ተቀብዬ ላቀብልሽ
ወይ ለማለት ነበር…በቃ ከሌለሽ ስትመጪ ይደርሳል ….እንደደረሽ ደውይልኝ››
‹‹አይ አሁን የባንክ ቁጥር ልክልሀለው…. በዛ ታስገባልኛለህ››
‹‹እሺ እንዳልሽ…››
‹‹አሺ ደህና እደር..ደግሞም ግልባጩ የፍንጥር ይሁን››
‹‹አረ ይበዛል››
‹‹አብሽር…..››
‹‹እሺ ይመቺሽ ሲሱ››
ስልኩ ተዘጋ..የእኔ አዕምሮ ግን ክፍትፍት እንዳለ ነው…ወሬቸውን ከመጀመሪያ
እስከመጨረሻው ሰምቼያለው..ግን ግራ ግብትብት እንዲለኝ ነው ያደረጉት..መጀመሪያ እዛ
እራት ላይ እያለን ሲደውልላት..ከወንዶች ጋር የሚያገናኛት ደላላ ነበር የመሰለኝ..አሁን ግን
የሚያወሩት ስለቢዝነስ ነው ..ስለ ዕቁብ ነው››
‹‹የባንክ ቁጥርህን ንገረኝ››ስትለኝ ከሀሳቤ ተነጠልኩ እና ትኩረቴን ወደ እሷ መለስኩ
‹‹የምን የባንክ ቁጥር….?››
‹‹ያንተን ነዋ››
‹‹ምን ሊያደርግልሽ….?››
‹‹አልሰማህም እቁብ ወጣልኝ እኮ….ብሩ አንተጋር እንዲቀመጥልኝ ፈልጌ ነው…50 ሺ ብር
ሰጥተኸኝ የለ..እኔ መቶ ልጨምርበት እና አንድ ላይ 150 ሺ ብር ይሆንልኛል››
‹‹አረ ምን አይነት ናላ አዞሪ ልጅ ነሽ….?››
‹‹እሺ ስጠኝ..እንደውም ተወው ..››አለችና ከመኝታዋ ተነስታ የጃኬቴን ኪስ ጎርጉራ የባንክ
ደብተሩን በማግኘት በስልኳ ቁጥሩን ጻፈችና እንዳለችው ለልጁ ልካለት መሰለኝ ተመልሳ
ወደ መኝታዋ ገባች….አዎ አብራኝ ትሄዳለች ማለት ነው ስል አሰብኩ…ደስስስስ አለኝ
‹‹ለመሆኑ ይሄን ሁሉ ብር ከየት አመጣሽው….?››
‹‹እቁብ..››
‹‹እሱንማ አወቅኩ …ግን ምን ሰርተሸ….….?መቶ ሺ ስተይ የሰማው መሰለኝ››
‹‹አዎ ትክክል ነህ..ሚኒባስ አለኝ…ሮማን በተለየዋት በወሩ ወዳ ሳይሆን ፈርታ ትገድለኛለች
ብላ ይመስለኛል የሻከረ ልቤን ምታለሰልስ መስሏት ሚኒባሱን በስሜ አዙራ
መለሳልኛለች››
‹‹ሚኒባስ..እና ስራውን ለምን አልተውሽም…….?››
‹‹እኔ እንጃ …ከሌብነት እና ከሽርሙጥና በስተቀር ሌላ ስራ ያለ ስለማይመስለኝ
ይሆናል….አንድ ለማኝን ከጎዳና ወስደህ በቀን ለምነህ የምታገኘውን ብር በእጥፍ አድርጌ
ሰጥሀለው አንተ ልመናውን ተውና እቤትህ ተቀመጥ ብትለው በአንዴ እርግፍ አድርጎ
የሚተው ይመስልሀል..….?ተደብቋ ወይም ሌላ ሰፈር ቀይሮም ቢሆን ይለምናል..ሌባ
ላመሉ ዳቦ ይልሳል ይባል የለ….
‹‹ደግሞ ስድስት ወር ሆኖኛል በሽርሙጥና የማገኘውን ብር ለገዛ ራሴ መጠቀም ካቆምኩ››
‹‹እና ምን ታደርጊዋለሽ….?››
‹‹…ፒያሳ ውስጥ ከሸሌ ተወልደው ግን እናታቸው የሞቱባቸው በየበረንዳውም በየዘመዱም
ተጠግተው የሚኖሩ ፈላዎች ሞልተዋል…ልክ እንደእኔ አይነት ዕጣ ላይ ህይወት አሸቀንጥራ
የወረወረቻቸው…..እና ከነዚህ መካከል ስምንት ሚሆኑትን ጋሼ ዜና እቤታቸው ያኖሯቸዋል…
ያላቻቸው ቤት ባለአንድ ክፍል ብትሆንም በተደራረበ አልጋ ላይ እዛ ያሳድሮቸዋል…ከዛ በላይ
ሊያደርጉላቸው ግን አቅም የላቸውም እራሳቸውም የሚኖሩት በሽራፊ የጡረታ ብር ነው…እኔ
ደግሞ በቀን አንድ ጊዜ ምሳቸውን እችላቸዋለው..ከዛ የቀረውን እነሱ ተሮሩጠው በመሸቀል
እና እርስ በርስም በመረዳዳት ህይወታቸውን ይገፋሉ… አንድ ደግ የፒያሳ ሀብታም ደግሞ
የትምህርት ቤት ወጪያቸውን ትችላቸዋለች..ሁሉም ይማራሉ …..ከትምህርት ቤት ከቀሩ
ድራሻቸውን ነው የማጠፋቸው…. ጋሼ ዜናም በትምህርት ቀልድ አያውቁም…. ፡፡››
‹‹እኔ አንቺ የምታወሪውን ነገር ሁሉ ለማመን በጣም እየተቸገርኩ ነው..ለመሆኑ በቀን አንድ
ጊዜ እየበሉ እንዴት ነው ትምህርት የሚገባቸው….ለዛውም ህጸናት ሆነው፡፡
‹‹እና በቀን ሁለት እና ሶስቴ ከበሉማ ምኑን ችግረኛ ሆኑ…..ይችሉታል..ላያስችል አይሰጥም
ይባል የለ….ድግሞ ሁሌ በቀን አንዴ ብቻ ነው የሚበሉት ማለት አይደለም…ግን ቢያንስ
ከጠፋ ከጠፋ በቀን አንዴ እስኪጠግቡ ይመገባሉ…››
‹‹እና አሁን ቅር ይላቸዋላ….?፡፡››
‹‹ለምን….?››
‹‹ማለት ሳትነግሪያቸው ስለመጣሽ››
‹‹አይ …የምግቡን ኮንትራት በወር አንዴ ነው ምዘጋላቸው…እንዲሁ ለአይናቸው ሲያጡኝ
ይናፍቁኝ ይሆናል እንጂ ሌላ ችግር የለውም….ደግሞ ነገ ልመለስላቸው አይደል….?››
‹‹በየሰከንዱ ነው እንዴ ሀሳብሽን ምትቀያይሪው..አብረን እንሄዳለን አላልሽም››
‹‹መቼ ነው እንደዛ ያልኩህ….….?ወጣኝ….?››
‹‹ብር ባንተ ደብተር ይግባልኝ እያልሽ አልነበር….?››
‹‹እሱማ ይገባልኛል››
‹‹እና አብረሺኝ ካልመጣሽ ..ብርሽ ምን ያደርግልኛል….?››
‹‹ይቀመጥልኛ››
‹‹በፍፅም …እኔ ባንክ አይደለውም››ኮስተር ብዬ
‹‹እንግዲያው ጥፋቱ ያንተ ነው …ሰራተኛ አድርገህ ቅጠረኝ አልኩህ..እንቢ አልክ››
‹‹አሁንማ ምኑን ቀጠርኩሽ..ይልቅ አንቺው ብትቀጥሪኝ ይሻላል…ለሚኒባስሽ ሹፌር
ስትፈልጊ ንገሪኝ››
‹‹የእወነቴን ነው ቅጠረኝ… ሰራተኛህ ልሁን››
‹‹እሺ››አልኳት ምን አጨቃጨቀኝ ብዬ ….እኔ ራሴ ምን መሆኔ ነው..ከዛ ህይወት ወጥታ
ከእኔ ጋር ለመኖር ትወስናለች ብዬ መጓጓቴ
‹‹ሶስት መቶ ብር ትከፍለኛለህ….?››
‹‹እከፍልሻለው›በወር ሶስት ቀን ትፈቅድልኛለህ….?››
‹‹አረ ለበፊት ለሰራተኛዬ በስድስት ወር አንድ ቀን ብቻ ነው ፍቃድ እሰጣት የነበረው…››
‹‹ስለዚህ አሻሽለው…››
‹‹ለመሆኑ ሶስት ቀን ምን ያደርግልሻል….?››
‹‹አዲስ አበባ እየሄድኩ ልጆቼን የማይበት.. የሚያስፈልጋቸውን ነገር የማሟላበት››
‹‹እንደዛ ከሆነ ተስማምቼያለው…››
‹‹እሺ ከነገ ጀምሮ የቤትህ ሰራተኛ የልጅህ ሞግዚት ነኝ…አሁን ለመጨረሻ ጊዜ እቀፈኝ››
ለመተኛት ትራሱንት አስተካክላ እየተዳለደለች … እኔ ተመሳሳዩን በማድረግና ለእንቀልፍ
እራሴን እያዘጋጀውና እሷንም እያቀፍኳት››
‹‹ለምንድነው ግን ማቀፌ የመጨረሻ የሚሆነው….?››
‹‹እንዴ የሄደችብህን ሰራተኛህ አቅፋህ ነበር እንዴ ምትተኛው….?››
‹‹በስመአብ ..ምን ለማለት ፈልገሽ ነው….? ››
‹‹ምንም.. ለማለት የፈለግኩት እኔም ከነገ ጀመሮ ሰራተኛህ ስለሆንኩ ላቅፍህም ሆነ
እንደዚህ ልስምህ አልችልም..ጭራሽ አብሬህም መተኛት አልችልም…›› ብላ ጉንጬን
ሳመችኝና.‹‹ደህ አድር›› ብላ አይኗቾን ጨፈነቻቸው..
እኔም ተንጠራርቼ መብራቱን አጠፋውና በስርአቱ አቅፉያት …ፀጉሯን እየዳበስኩ ወደ
እንቅልፍ ሳይሆን ወደ ማሰላሰል ውስጥ ገባው..እውነት ያለችው ነገር ከምሯ ሆኖ አብራኝ
ትሄድ ይሆን ….….?መቼስ ሰራተኛህ እሆናለው የምትለው የአመቱ ታላቁ ቀልድ መሆን
አለበት…ነግቶ የሚፈጠረውን ነገር ለማወቅ ቸኮልኩ..ይዤት ወደ ሀገሬ እበራለው ወይስ
እሷን በሚኒባስ ወደ አዲስ አበባ አሳፍሪያት እኔ በሀዘን እና በትካዜ ወደ ልጄ
እሄዳለው…..እስከዛሬ ለአመታ የኖርኩት ብቸኝነት አሁን አስፈራኝ…እንዴት ነበር ያን ሁሉ
አመት ያለ ፍቅር ያሳለፍኩት…….?ትታኝ ስትሄድ እንዴት ነው የምሆነው…….?አንዴት ነው
ዳግመኛ ማጣትን የምቋቋመው….….?ከእንቅልፌ ስባንን ሰዓቱ ንጊት አካባቢ ሆኖ ነበር…አስራ አንድ ሰዓት ተኩል…ቀስ ብዬ
ተጠንቅቄ መብራቱን አበራውት..ጄጄ ደረቴ ላይ ሽብልል ብላ የሰላም እንቅልፋን
እየለጠጠችው ነው፡፡አትኩሬ በጽሞና አስተዋልኳት…ፊቷ ላይ ፍጽም ሰላም እና መረጋጋት
ነው የሚነበበው…በዛ ሁሉ መከራ በዛ ሁሉ ስቃይ ውስጥ ያለፈች አትመስልም…በፍፅም …
አረ እንደውም አሁን እንዲህ ሳያት ከቤተሰብ ጉያ ወጥታ የማታውቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ቤርጎ
ያደረች…ለማጀመሪያ ጊዜ ከእኔ ጋር የተኛች ነው የምትመስለው….
ጉዴ ፈላ… ይህቺን ልጅ በጣም ነው ያፈቀርኳት..አሁን እትኩሬ ሳያት እንኳን እንዴት የልቤ
ምት እንደጨመረ..እንዴት ደሜ በውስጤ ሞቆ መንተክተክ እንደጀመረ እኔ እና እግዜር ብቻ
ነን የምናውቀው…..አዎ ይህቺን ልጅ ከዚህ በላይ ላቅፋት ነው የምፈልገው ….ይቺን ልጅ
ከአዚህ በላይ ነው ልንከባከባት የምፈልገው….ይህቼን ልጅ ከዚህ በላይ ነው ልዋሀዳት
የምፈለገው….ይህቺን ልጅ ለዘላለሙ ነው አብሬያት መኖር የምፈልገው፡፡
ይገርመኛል ስለማንነቷ በአይኔ ያየዋቸው ከእሷም የሰማዋቸው ነገሮች እና በውስጤ ደግሞ
ስለእሷ የማስበው ፍጽም የተለያየ ነው….እንዴት ነወ ሰው በአይኖቹ ያየውን ነገር ላለማመን
የሚችለው…. ዛሬ አንድ አልጋ ላይ በእንዲህ አይነት ሁኔታ ተቃቅፈን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ
ተጣብቀን ስንተኛ ለሶስትኛ ለሊት ነው…በዚህ ሶስት ቀን ሙሉ ግንኙነታችን በመንፈስ
መቆራኝታችን በብዙ እጥፍ ቢያድግም በአካል ቁርኝት በኩል ግን ከሶስት ቀን በፊት ያለበት
ቦታ ነው ያለው…ያገኘዋትም ቀን እንዲህ እሷ ከእነ ልብሶ እኔ ደግሞ እራቁቴን ተቃቅፈን
ነበር የተኛነው..ዛሬም በሶስተኛው ቀን በተመሳሳይ ሁኔታ ነው ተኝተን የምንገኘው…
…….እና እሷ ስለነገረቺኝ ነገር አይደለም ውስጤ እያሰበ ያለው…. ባሳለፈችው ህይወት
የተነሳ ወንዶች ላይ ባለት ጥላቻ የተነሳ እኔን ላለመጥላት ወደ ወሴባዊ ግንኙነት መግባት
እንዳማትፈልግ የነገረቺኝን አይደለም እያሰብክ ያለውት….ድንግል ሰለሆነች..ከዚህ በፊት
ወንድ ስለማታውቅ ፈርታ ወይም አፍራ እንቢ ያለቺኝ እና በድንብ ስትለምደኝ ሁሉ ነገሯን
ስትደብቅ እና ሳትሰስት ግልጽልፅ አድርጋ እንደምትሰጠኝ ነው የማስበው …፡፡ማልመውም
እንደዛ ነው…እንጂ እሷ ለእኔ አምስት አመት በውሲብ ንግድ ያሳለፈች ….በሺ ወንዶች
ወሲባዊ ላብ የወረዛች…ለሺ ቅንዝራም ወንዶች ጭኖቾን ያስጎበኝች…ከሺ ወንዶች ጋር
ተዳርታ መቶ ሺ ብሮችን የሰበሰበች....ከእድሜዋ እጥፍ የኖረች የችግሮች ማከማቻ..
የመከራ ጎተራ እንደሆነች ባውቅም ያንን እንዴት ማሰብ እችላላው..?በምንስ አቅሜ በዛ
አይነት ምስል እሷን ልሳላት እችላለው..?፡፡አዎ የሰማውትም ያየውትም ይሄንን ነው
..ውስጤ ግን እንዲህ አይደለም የሚያስበው… ልክ እንዷ ልጄን በምወዳት መጠን
ልወዳት..ልክ ልጄን በምጠብቅበት መጠን ልጠብቃት… ልክ የልጁን የነገ ህይወት
ለማሳመር በምጥርበት መጠን ለዚህችም ልለፋላት እፈልጋለው….ረዳት አልባ እና ደካማ …
ማረፊያ ጎጆ የሌላት ወፍ አድርጌ ነው የማስባት….አውቃለው እውነቱ ይሄ አይደለም..
እሷ… ይህቺ ክንዴን ተንተርሳ አንገቴ ውስጥ ተወሽቃ የተኛችው ልጅ ጥንካሬዋ ከአልማዝ
በላይ… በራስ መተማመኗ ከነገስታቶች የበለጠ...መከራ ማይበግራት…ችግር ጠምዝዞ
የማይሰብራት…ለወደደችው ህይወቷን እስከመስጠት የምትሰዋ.. የጠላችውን ህይወቱን
ለመቀማት ድፍረቱና ፅናቱ ያላት…የተራራ ግዝፈት እና ውቅያኖስን የሚያህል ጥልቀት
በሚጢጢ ልቧ ተሸክማ የምትዞር ልዩ ልጅ እንደሆነች አውቃለው….
እውነታው እሷን ለመጠበቅ..እሷን ለመንከባከብ ሳይሆን በእሷ ለመጠበቅ እና በእሷ
የእንክብካቤ ጥላ ውስጥ ለመሸሸግ የፈለኩት እኔ እራሴ ነኝ..በህይወቴ ውስጥ
የተተከለውን ስር የሰደደ ፍርሀት እንድታክምልኝ ነው የፈለኳት..በብቸኝነት እና በፍቅር እጦት
የሚዳክረውን ልፍስፍሱን እኔነቴን እንድትጠግንልኝ እና እንድታበረታልኝ ነው የፈለኳት ..ለገዛ
ሀጃዬ..ለገዛ ደንታዬ..አዎ እወነታው ያ ነው፡፡
1፡20 ላይ ባላችበት እጆቾን ዘረጋግታ ተንጠራራችና ቀስ በቀስ ዓይኖቾን ገለጠቻቸው
‹‹..አዎ ከነቃው ሁለት ሰዓት ሊሆነኝ ነው››
‹‹ሁለት ሰዓት ታዲያ ለምን አልቀሰቀስከኝም…..?ረፍዷል እኮ››
‹‹በተመስጦ እና በፍዘት እያየሁሽ …እንዴት እንደምታምሪ ከጨረቃ ውበት ጋር እንኳን
መዳደር እንደምትቺይ እያሰብኩ… በመደመም ላይ ሰለነበርኩ የሰዓቱ ርዝመት
አልታወቀኝም….››
‹‹ወሬ አለብህ…በል ተነስ››ብላኝ ቀድማኝ ተነሳችና ወደ መታጠቢያ ክፍል ገባች፡፡
ተነሳውና ልብሴን መለባበስ ጀመርኩ..እሷም መጣችና ከላይ የለበችውን ቲሸርት
አወለቀች…ያ እንደሰነፍ ገበሬ የእርሻ መሬት በተወለጋገ ጠባሳ እና ሰንበር የተሞላ ግማሽ
ሰውነቷን ዳግመኛ ፊት ለፊት ስትገትር ስቅጥጥ አለኝ….ደግነቱ ቶሎ ብላ ማታ የገዛውላትን
ቀሚስ አነሳችና ለበሰች…ተንፈስ አልኩ..ቀጠለችና ለብሳ ያደረችውን ሱሪ በማውለቅ
ፔስታል ውስጥ ጨመረችው…ሙሉ ዝግጅታችንን ጨርሰን ቤርጎውን አስረክበን ለመውጣት
15 ደቂቃ ብቻ ነበር የፈጀብን፡፡
ወደ ሚኪናችን እያመራን ነው..የልቤን ምት አትጠይቁኝ.. ተፈጥርቃ በአፌ ልትወጣ
እየተንፈራገጠች ነው…የሞት ፍርድ ተፈርዶበት ወደ መሰቀያው ወይም ወደ መቀያው
በፖሊስ ታጅቦ የሚሄድ ፍርደኛ በመጨረሻው ደቂቃ የሚሰማው አይነት ስሜት ነው
እየተሰማኝ ያለው…የእውነት አሁን አብራኝ ትሄዳለች…የእወነት ዛሬ ይህቺ ልጅ የእኔ ልትሆን
ነው….የእውነት ቀዝቃዛ አንሶላ ለብሼ በድን ትራስ ታቅፌ የምተኛበት ያለፈ የብቸኝነት
ህይወቴ መቋጫ ሊያገኝ ነው…
ገቢናውን ተንደርድሬ ከፈትኩላት..በዝምታ ገባችና ቁጭ አለች..ተመስገን ነው…ይህ
መልካምና የብሩህ ዕድል ብርሀናማ ምልክት ነው..አብራኝ ባትሄድ ኖሮ መኪናው ውስጥ
አትገባም ነበር፡፡ግን ለምንድነው የጨገጋት .. ..?ግን ለምንድነው ፊቷ ኮሶ እንደጠጣ ሰው
እንዲህ በጥዋቱ የተኮሰታተረው…....?ምን አይነት የሰነፍ ጥያቄ ነው እራሴን እየጠየቅኩ
ያለውት…...?ወደ ማታውቀው ሀገር እኳ ነው የምትሄደው… ተወልዳ ያደገችበት 19 አመት
የኖረችበትን ፒያሳን የመሰለች ያራዶች መንደር እኮ ነው ጥላ ልትሄድ የወሰነችው….
ብዙ ጓደኞቾን እና ብዙ ትዝታዎቾን እኮ ነው ለእኔ ስትል በመታው ወደ ማታውቀው ሀገር
ከማታውቃቸው ሰዎች ጋር ለመኖር የምትሄደው..እንደውም እሷ ስለሆነች እንጂ ሌላ
ልፍስፍስ እና ስሜተ ድፍርስ ሴት ብትሆን ኖሮ ይሄኔ ከመኮሳተር እና በዝምታ ከመሸበብም
አልፋ በእንባ ትታጠብ ነበር…በሽራፊ ሰኮንዶች ውስጥ ነው ይሄንን ሁሉ ያሰብኩት… ገቢና
ገብቼ የሹፌሩን ቦታ በመያዝ መኪናውን በማስነሳት ሞተሩ እስኪሞቅ እየጠበቅኩ
ባለውበት ሽራፊ ሰዓት…..
መኪናዋን አንቀሳቀስኩና ወደ በሩ እንቅስቃሴ ጀመርኩ.‹‹እርቦኛል›› አለቺኝ…ከሩቅ የተለቀቀ
በሚመስል የደከመና እና የተጎተተ ድምጽ
‹‹ምን ችግር አለው....?ቁርሳችንን በልተን ጉዞችንን መቀጠል እንችላለን››አልኳት ከግቢው
እየወጣን
‹‹ወደእዚህ ይሻለናል ወይስ ወደእዚህ....?››ደህና ቁርስ የምናገኘው በየትኛው አቅጣጫ
ብንሄድ እንደሆነ ከእሷ ምክር እየጠየቅኩ ነው…ምክንያታዊ ሳይሆን ግምታዊ ምክር
እንድትሰጠኝ…የነቀምትና አቅጣጫ ተወችና ወደ አዲስ አበባ አቅጣጫ በእጆ ምልክት
ሰጠቺኝ…የመኪናዋን አቅጣጫ ወደ እዛ አዞርኩት…የተከፈተ ቁርስ ቤት ከአስፓልቱ ግራና
ቀኝ እያየንበዝግታ እነዳው ጀመር..ግን ስራ የጀመረ ወይም የተከፈተ ቤት ለማግኘት
መነኸሪያው ድርስ መጓዝ ነበረብን…ከመነኸሪያው በተቃራኒ መንገዱን ተሸግሮ ካለ ህንጻ
ምድር ቤት ያለ ካፌ ተከፍቷል፡፡አንድ አምስት የሚሆኑ ደንበኛች በረንዳ ላይ ቁጭ ብለው
ቁርስ ሲበሉ እና ትኩስ ነገር ሲጠቀሙ ይታያሉ… ወደ እዛው ነዳውና መሪዬን ጠምዝዤ
የመኪናዋን አፍንጫ ወደመሄጃችን ወደ ጉደር አቅጣጫ አዙሬ አቆምኩና
‹‹..በይ እዚህ እንብላና መንገዳችንን እንቆስቁስ››አልኳት
‹‹እሺ›› አለችና ፔስታሏን ይዛ ልትወርድ ተዘጋጀች….. ግራ ገባኝ ..በጣም
ደነገጥኩ..የድንጋጤ ግራ መጋባት፡፡
‹‹ምን ያደርግልሻል….....?ፔስታሉ ይቀመጥ እንጂ››
ትቃወመኛለች ብዬ ስጠብቅ…‹‹እሺ›› አለችና ፔስታሉን ከፍታ ጅንስ ሱሪያዋን አወጣችና
ከኪስ ውስጥ አነስተኛ የኪስ ቦርሳዋን በማውጣት ሱሪውን ወደ ፔስታሉ መልሳ ከታ
ወደነበረበት በመመለስ በአንድ እጇ የኪስ ቦርሳዋን በሌላ እጇ ሞባይሏን በመያዝ.‹‹.ቁርስ
ገባዦ እኔ ስለሆንኩ ገንዘብ ልያዝ ብዬ ነው››ብላኝ መኪናውን ለቃ ወረደች፡፡
የእፎይታ ትንፋሽ ተንፍሼ እኔም ከመኪናው ወረድኩና ቆልፌ ተከተልኳት
‹‹አንድ እንቁላል በስጋ እና አንድ ዱለት››አዘዝኩ
‹‹ አንድ ምግብ ይበቃ ነበር››
‹‹ምነው ከፋይ አንቺ ስለሆንሽ ቆጨሽ እንዴ..?››
‹‹አይደለም ..ጥዋት ስለሆነ አፒታይቱን ከየት እናመጣዋለን ብዬ ነው››አለቺኝ
‹‹ግድ የለሽም የቻልነውን ያህል እንሞክራለን..››አልኳት…..ወዲያው ሳናስበው ወደ
ዝምታችን ተመለስን…ሁለታችንም አንድ የፈራነው ነገር እንዳለ ያስታውቅብናል…ይህቺን
ከተማ መልቀቅ…ወደ ሻንቡ መብረር…ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገር…..
አንድ ልጅ እግር ሴት አንድ አመት የሚሆነው ሕጻን ልጅ የታቀፈች ከጎናችን
ተቀምጣለች….ልጇ በጣም እየረበሻት ነው…..በሀይለኛው ያለቅሳል..ዝም እንዲልላት
ልታባብለው እየሞከረች ነው…..ግን በዋዛ ሚደለል ልጅ አልነበረም….እፍ ውስጥ ጡጦ
ለማስገባት ትሞክራለች… ተንፈራግጦ ከአፉ ውስጥ በምሬት ያወጣል..
‹‹ምን ሆኖ ነው..?››አለቻት …እንደእኔ በልጁ ሁኔታ ቀልቧ የተሰረቀባት የእኔዋ ጂጂ
‹‹ጡት ስጪኝ እያለ ነው መከራዬን የሚያሳየኝ››
‹‹ጡት…!!!!››ግራ ገባኝ..አይኖቼን ወደ ደረቷ ላኳቸው… ዱባ ሚያካክሉ ግዙፍ ጡቶች
በደረቷ ግራና ቀኝ ይታዩኛል
.‹‹እና ለምን አታጠቢውም....?እናቱ አይደለሽም እንዴ....?ጡትሽ እንዳይወድቅ ፈራተሽ
እንዳይሆን....መቼስ ዘመኝኛ ሴቶች እራስ ወዳድነታችው ቅጥ እያጣ ነው››አልኳት
‹‹የልጅቷ ፊት በአንዴ ቅይርይር አለ…አይኖቾ በእንባ ተሞሉ..አረ ለቀቀችው….ልክ እንደነሀሴ
ጅረት መስመር እየሰራ በጉንጮቾ ላይ እየተንኳለለ..መርገፍ ጀመረ….ደነገጥኩ..በጣም
ደነገጥኩ
‹‹ምን አይነት ቀሺም ነህ....?የት ታውቃታለህ እንዲህ ምትዘባርቀው…..?››ጂጂ በእኔ ላይ
አውሬ ሆነችብኝ፡፡ደነገጥኩ፡፡
‹‹እኔ እኮ ስቀልድ ነው..እህቴ ይቅርታ… ማይኆን ነገር ዘባረቅኩ እንዴ..?››
‹‹ልጇን ማጥባት የማትፈልግ እናት እንዳለች እኔ አላውቅም..ለሌቱን ሙሉ እንቅልፋ በአይኔ
ሳይዞር ነው የደርኩት..እንዲመገብልኝ ያልሞከርኩት የህጻናት ምግብ አልነበረም …
ከማልቀስ በስተቀር አንድንም አልቀመሰልኝም..እና ይሄን ያህል በልጄ ምጨክን
ይመስልሀል..?፡፡››እየተነሰቀሰቀች በምሬት ተናገረች፡፡
‹‹አይዞሽ ተረጋጊ…ምን ሆነሽ ነው..?፡፡››ጅጅ ነች ልታረጋጋት እየሞከረች በሀዘኔታ
የጠየቀቻት
አሞኝ ከዋዩ ከተማ ነው ለህክምና የመጣውት …የጡነቀርሳ እንዳለብኝ ከሶስት ቅን በፊት
ነው የተነገረኝ…ለልጄ ጡት ማጥባቱት እንዳቆም አጥብቀው ነግረውኛል…እሺ ምን
ላድርግ….አሁን እዚህ የተቀመጥኩት ወድጄ መሰለህ..ጨንቆኝና የማደርገው ጠፍቶኝ
ነው..ዝም ቢልልኝ ብዬ ለመሞከር ነው….ልጇን አቀፈች… እቃዋን ሰበሰበችና መቀመጫዋን
ለቃ ወደ ታች መንገዷን ቀጠለች..ከአይኔ እስክትጠፋ በዓይኖቼ ሸኘዋት
…ምንም ልል አልቻልኩም..በጣም ነው በራሴ ያፈርኩት…እውነትም ጂጂ እንዳለችው ምን
አይነት ቀሺም ነኝ፡፡
‹‹በጣም አዝናለው..ልጅ ግን ወተት መጥባት ማለት ጡጦውን ለምንድነው እንዲህ
አልጠባም ብሎ ሚያሰቃያት፡፡
‹‹ወላጅ አይደለህ እንዴ ..?ስለእናት ጡት እና ስለ ላም ወተት ልዩነት አታውቅም....?የእናት
ጡት በሜኔራልና መአድን የበለፀገ እረሀብ ማስታገሻ ምግብ ብቻ አይደለም……የእናት ጡት
ከወተትነቱ ባሸገር ከእናቲቱ ልብ ከመነጨ ፍቅር ጋር የተቀየጠ የመንፈስ ምግብም ጭምር
ነው…ለዛ ነው የእናት ጡት ለህጻኑ ሙሉ ጤንነት የሚያጎናፃፈው …ለዛ ነው የእናቱን ጡት
በበቂ መጠን የጠባ ልጅ ዕድሜውን በሙሉ በአካልም በመንፈስም ፅኑና ጠንካራ
የሚሆነው..
አንድ ህጻን ልጅ የእናቱን ጡት ከላም ወተት ብዙ እጥፍ እስበልጧ የሚወደውና
የሚፈልገው የእናት ጡት የበለጠ ጣፋጭ ስለሆነ ይመስልሀል..አይደለም የእናት ፍቅርም
አብሮት እየተቀየጠ ስለሚፈስለት ነው….አንድን ህጻን በደህንት ከኖረበት የእናቱ መህጽን
ወጥቶ ከእናቱ የሚያገናኛው እትብቱም ሲበጠስበት በደመነፍስም ቢሆን ያዝናል
ያለቅሳል..ግን ያንን የሚያካክስለት ጡት ነው… ቀጥታ የእናቱን ጡት አፍ ውስጥ ሲገባ
በእትብቱ ምትክ ከእናቱ ሚገናኝበት የፍቅር ድልድይ ይሆንለታል…
‹‹ገባኝ..››አልኩ ከመግባትም በላይ ገለጻዋ እየገረመኝ..ቁርሱ ቀረበ… በቅጡ ግን
አልበላነውም …ሁለታችንም የምግብ ፍላጎታችን ቁልፍልፍ ብሎ ነበር..እንደነገሩ ቀማምሰን
ከጨረስን ቡኃላ ሂሳብ ከፈለች..ከዛ ድንገት..ፈጠን ብላ ቀድማኝ ተነሳች ወደ… እኔ
ቀረበች… ጉንጬን ጠበቅ አድርጋ ሳመችኝና ..ምንም ሳትናገር..ፊቷን አዙራ መንገዷን
ቀጠለች….አፌን ደም ደም አለኝ…..ምን እያደረገች ምን እየሆነች እንደሆነ መገመትም
እልቻልኩም….ከመቀመጫዬም አልተነሳውም..በተቀመጥኩበት ደንዝዤ በአይኔ ብቻ
እየተከተልኳት ነው..ዞር ብላም አላየችኝ..እንዳቀረቀረች በተጓተተ እርምጃ ቀጥታ እስፓልቱን
ተሸገረች… ሄደች …. ተጠመዘዘች..መነኸሪያ ጊቢ ውስጥ ገብታ ከእይታዬ ተሰወረች፡፡
እውነትም ይህቺ ወፍ ነች…የፒያሳ ሚስጥራዊ ወፍ……ምን ያህል ጊዜ እዛው ትታኝ የሄደቺኝ ቦታ ከነ ድንዛዜዬ እንደቆየው አላውቅም....ምን ሰዓት
ላይ መቀመጫዬን ለቅቄ መኪናዬ ውስጥ እንደገባውም ትዝ አይለኝም…ጉደርን አልፌ
ተራራማ እና ጠመዝማዛውን መንገድ ተያይዤው ጌዶ ከተማ ልገባ ሀያ ኪሎ ሜትር አካባቢ
ሲቀረኝ ነው በመጠኑ ወደ ቀልቤ የተመለስኩት..
ቆይ ግን ሳላውቅ ያስቀየምኳት ነገር ይኖር ይሆን እንዴ…..?ሁሉ ነገር በሳለም እየተጓዘ
አልነበረ እንዴ…..?ለሊት በእንቅልፍ ልቤ በማይሆን መልኩ የማይሆን ቦታ ነካክቼያት
ስሜቷን እስቆጣዋት ይሆን እንዴ..?ምንም ትዝ ሚለኝ ነገር የለም፡፡ነው ወይስ ያቺኝ እናት
ለቀልድ ብዬ የተናገርኩት ነገር ለእኔ ያላትን አመለካከት እንድትቀይር አድርጓት
ይሆን..?..አይ እንደዛማ አይሆንም…ለቀልድ ብዬ ባዳለጠኝ የምላስ ወለምታ ያን ሁሉ ፍቅር
..ያን ሁሉ ተስፋ እንዲህ በአንዴ ገደል አትከተውም..አዎ በፊቱንም ውሳኔዋ ወደ ፒያሳዋ
መመለስ ይሆናል
…አዎ እንደዛ ነው..እንደዛ መሆኑ ደግሞ ያንገበግባል…….አካባቢዬን ቃኘው …የት
እንደደረስኩ ሳውቅ ግርም አለኝ…እንዴት እንዴት ነው የነዳውት....?እንዴትስ ከሌላ መኪና
ጋር ሳልጋጭ....?ያስ ባይሆን እንዴት መንገድ ስቼ ወደ አንዱ ገደል ያልተሸቀነጠርኩ…...?ዝ
ግንን አለኝና አማተብኩ..አማትቤ ዞር ስል ከጎኔ ያለው መቀመጫ ስር ፔስታል አየው …
መኪናውን መንዳቴን ሳላቋርጥ ተንጠራራውና አነሳውት … አዎ የእሷ ቲሸርት እና ጄንስ ሱሪ
ነው…በመስኮቴ አሻግሬ ወደ ቁልቁለቱ ጫካ ውስጥ አርቄ ወረወርኩት….
እንኳን ቡትቶዋን ምኗንም አልፈልግም….አትረባም…እንዴት እንደዚህ ታደርገኛለች…..?
እንዴት እንደዚህ እንደህጻን ልጅ ታታልለኛለች…..?በእሷ ቤት እኔ የገጠር ልጅ ፋራ እሷ
የፒያሳ ልጅ አራዳ መሆኖ ነው….፡፡እሰከአሁን ለሶስት ቀን ስትደበርብኝ ነበር ማለት ነው…..?
ስለእሷ ማሰብ አልፈልግም፡፡›..ፎከርኩ …ግን ውስጤ አሁንም እየተቃጠለ ነው…የሆነ ሹል
ጦር መሳይ ነገር ልቤን እየሰቀሰቀኝ ነው…እና ደግሞ ድክምና ስልምልም እያደረገኝ ነው
…..እናንት በአንዴ መኖር እንዲህ ያስጠላል እንዴ…..? ግን ከዚህች ልጅ ጋር ያሳለፍኩት
ሶስት አመት ነው ወይስ ሶስት ቀን…....?ግራ ግብት አለኝ ፡፡ የእውነቴን እኮ ነው..በሶስት
ቀን ትውውቅማ እንደዚህ ብትንትኔ አይወጣም..እንደዚህ ፍርክስክስ አልልም….፡፡
ልጄ በጣም ናፈቀቺኝ ..መኪናዋ እንደፕሌን ክንፍ ኖሯት በአየር ላይ ብትበርልኝ እና ፈጥኜ
ሾንቡ ብደርስ ደስ ይለኝ ነበር..አሁን የሚያጽናናኝ የልጄ ፈገግታ ብቻ ነው..አሁን ሊያረጋጋኝ
የሚችለው የልጄ ትንፋሽ ብቻ ነው…ውስጥ እግሬን ሁሉ እያቃጠለኝ ነው…፡፡
….ጌዶ ደረስኩ… ዝምብዬ ከተማውን ሰንጥቄው ላልፍ አልኩና ቢያንስ እያቅለሸለሸኝ
ያለውን ነገር ያስታግስልኝ እንደሆን ጥቁር ቡና ልጠጣበት ፈለኩ… መኪናዬን አንድ የጀበና
ብና የሚሸጥበት ቤት አጠገብ አቆምኩና ወርጄ ብና አዘዝኩ…እየጠጣው እያለው ሞባይሌ
ድምጽ አሰማች… ተደውሎልኝ አይደለም…የመልዕክ መጥቶልሀል አብሳሪ ድምጽ
ነው..በግዴለሽነት ከፈትኩት…አፌውስጥ የነበረው ብና ወደ ስርኔ ሾለከ… ትን አለኝ
..እየጠጣው ያለውትን ሲኒ በድንጋጤ ለቀቅኩት …አካባቢው ያሉት ሰዎች ሁሉ
በረገጉ‹‹..አይዞህ…እኔን…ውሃ ጠጣበት››ሁሉም ሊያጽናኑኝ ሞከሩ …ማንንም አልሰማው…
ከኪሴ 5 ብር አወጣውና ጠረጵዛ ላይ አስቀመጬ ቦታውን ለቅቄ ሄድኩ …መኪናዬ ውስጥ
ገባው……
ሞተሩን አስነሳውና የመኪናዬን መሪ ጠምዝዤ አዞርኩ..ወደ መጣውበት ተመልሼ መንዳት
ጀመርኩ..በቃ ላብድ ነው….በትክክል እያበድኩ ነው……ይህቺ ልጅ እያሳበደቺኝ ነው….ሀያ
ኪሎ ሜትር ያህል ነዳው አቆምኩ…እና መንገዱን ተሸገርኩ…ከመኪናዬ ወረድኩና ቀስ ብዬ
በጥንቃቄ ገደሉን ወደ ታች እየተንሸራተትኩ ወረድኩ….ጫካ ውስጥ ገባው … እሾክ
ይወጋኛል አውሬ ያገኘኛል ብዬ ሳልጨነቅ ማሰስ ጀመርኩ… አዎ አገኘውት ..፡፡ተበታትኗል …
ጂንስ ሱሪው ለብቻው የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ ተንጠልጥሏል… ቲሸርቱ ደግሞ ለብቻው መሬት
ላይ ተነጥፎ አገኘውት… በፈገግታ ሁለቱንም ከያሉበት አንስቼ ያዝኩ… ፔስታሉን ለማግኘት
ግን አልተሳካልኝም..ምን አልባት ንፋስ ወስዶት ይሆናል…አላስጨነቀኝም ..፡፡በዳዴ የመሄድ
ያህል እየቧጠጥኩ አቀበቱን ወጣው..ለካ መውጣት የመውረድን ያህል አይቀልም
…..ከወጡ መውረድ የሚከብደው ለካ ተመልሶ መውጣት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ
ከልምድ ስለሚታወቅ ነው፡፡
….እያለከለኩ ወደ መኪናዬ ሄድኩና ገቢና ገባው…ሱሪውን በስነስርአትና በጥንቃቄ
አጣጠፍኩ… ቲሸርቱንም በተመሳሳይ አጣጣፍኩት ..በፍቅር ወደ አፍንጫዬ አስጠግቼ ወደ
ውስጤ ማግኩት..በጣም በጥልቀት ሳብኩት..ጠረኗን ለማግኘት..አዎ ጠረኗ ወደውስጥ
ከማግኩት አየር ጋር ተቀላቅከሎ ወደ ውስጤ ገብቶ በሰውነቴ ውስጥ በመበተኑ እያንዳንዱ
የሰውነቴ ሴል ሲነቃቃ እና ሲፍታታ ታወቀኝ…ልብሱን ቦርሳዬ ውስጥ ከእኔ ልበሶች ጋር አንድ
ላይ አስቀመጥኩት… መኪናውን አንቀሳቀስኩ ቦታው ለማዞር ስለማይመች ሰፋ ያለ ቦታ
ለማግኘት የተወሰነ መንገድ ወደ ፊት መንዳት ነበረብኝ… ብዙ ተቸግሬ ነው ያዞርኩት….አሁን
ጭልም ባለ ሳይሆን በጭላንጭል ቢሆን አጨንቁሮ በሚታይ ተስፋ በመረጋጋት እየነዳው
ነው ..ተመልሼ ጌዶ ደርሼያለው….ዋናውን የአስፓልት መንገድን ለቅቄ ወደ ቀኝ ታጥፌ
የሻንቡን መንገድ ይዤያለው…አሁን እንደቅድሙ ቡና አላማረኝም ከተማዋን ሰንጥቄ
አለፍኩ….
ወይኔ የእኔ ነገር እንዲህ ያደረገኝ ምን እንደሆነ ሳልነግራችሁ… ..ማለት የጽሁፍ መልዕክት
ከባንክ ቤት ነው የተላከልኝ … የባንክ ደብተሬ ውስጥ 100 ሺብር እንደገባልኝ ሊነግሩኝ
ነው…ብሩ ወደ እኔ መላኩ አንድ ጭልም ያለ ተስፋዬን በመጠኑ አለምልሞልኛል..መቼም
ልታገኘኝ ባትፈልግ ኖሮ ብሩን አትልክም ነበር…የሚል ሀሳብ በውስጡ እንዲጸነስ ምክንያት
ሆኗል… ለዛ ነው ወደኃላ የተመለስኩት..አንድ ቀን ማለቴ በቅርብ..ነገ ወይም ተነገ ወዲያ
መጥታ ሱሪዬስ ስለትለኝ ጥዬዋለው ልላት ድፍረቱን ከየት አገኛለው… ለዛ ነው የጣልኩትን
ልብሷን ፍለጋ ወደ ኃላዬ ያን ሁሉ መንገድ የተጓዝኩት…..…
ግን ይህቺን ልጅ እኮ ላምናት አልችልም …..ብሩን ወደ እኔ ደብተር ማስገባት ያሰበችው
ቁጥሩንም ለልጁ የላከችለት ትናንት ማታ ነበር..ማታ ደግሞ ለእኔም ብዙ ነገር ብላኝ ነበር…
አብራኝ እንደምትመጣ…ለልጄ እናት መሆን እንደምትፈልግ ቃል ገብታልኝ ነበረ… ግን
አላደረገችውም..የማታ ንግግሯን ሙሉ በሙሉ ሰርዛዋለች..ታዲያ ይሄንንስ ለልጁ ማታ
የነገረችውን ነገር እንዳያደርገው መንገሩን ዘንግታው ቢሆንስ …..?ይሄንን ሳስብ ከእንደገና
በሰውነቴን ጥልቅ ድረስ ቅዝቃዜ ተሰራጨብኝ..ትንፋሼን ወደ ውስጥ መሳብ
አቃተኝ…..ወይኔ ሰውዬው … !!!!መኪናዋ ወዲህና ወዲያ ጆካ ማምታት ጀመረች…
እንደምንም በደመነፍስ ፍሬን ይዤ አቀዘቀዝኩና አቆምኩ…..መሪው ላይ ተደፍቼ ለመረጋጋት
መክርኩ…አስር የሚሆኑ ደቂቃዎችን በደነዘዘ ስሜት ካሳለፍኩ ቡኃላ ስልኬን አነሳው…
ደወልኩላት..በአራተኛው ጥሪ ተነሳ….
‹‹ሄሎ..››
ቀጥታ ወደ ጉዳዬ ገባው‹‹ ልጁ ብሩን ተሳስቶ አስገብቶታል››
‹‹የቱን ብር..?››የደነገጠ እና የሚርገበገብ ድምጽ ተሰማኝ..ከሰማውት ድምጽ በእጥፍ
የእኔም...ድንጋጤ ጨመረ…
‹‹አይዞሽ…የባንክ ቁጥርሽን ላኪልኝና አሁን ዋዩ ወይም ፊንጫአ ስደርስ መልሼ
ልክልሻለው››
‹‹ምኑን ነው ምትልክልኝ..?››
‹‹መቶ ሺ ብሩን ነዋ…ደብተሬ ውስጥ እንደገባ አሁን በሚሴጅ አሳውቀውኛል››
‹‹…እ እሱን ነው እንዴ....?››ብላ ሌላ ቅዝቅዝ ያለ ስሜት ውስጥ ከተተቺኝ
‹‹አዎ..በሚሴጅ የባንክ ቁጥርሽን ላኪልኝ››
‹‹የባንክ ደብተር የለኝም…አንተ ጋር እንዲቀመጥልኝ ነው ያስላኩት››
‹‹ለምን..?››
‹‹እንዴት ለምን .. ..?ይቀመጥልኛ፡፡››
‹‹ይቀመጥልኝ ማለት .. ..?ትመጪያለሽ …..?ማለት ብርሽን ልትወስጂ››
‹‹በህይወቴ ወሳኝ የሆነ አንድ መፈጸም ያለብኝ የረጅም ጊዜ ዕቅድ አለኝ….ያንን ጉዳይ
በዕቅዴ መሰረት ለመፈፀም ከአስር እስከ ሀያ ቀን ይፈጅብኛል..ከተሳካልኝ ወዲያው
እመጣለው…ማለቴ ብሩ ጋር ሳይሆን አንተ ጋር..ይቅርታ አንተ ጋር ሳይሆን ልጅህ ጋር…
ልጅህን ልጄ ላደርጋት…..››
‹‹እቅድሽ እንዳሰብሽው ካልተሳካልሽስ..?››
‹‹ካልተሳካልኝማ አልተሰሳካልኝም ማለት ነው..ከዛ ቡኃላ እኔም የለውም ማለት ነው››
‹‹አልገባኝም..?››
‹‹በቃ.ጂጂ የምትባል ልጅ የለችም ማለት ነው..እስከ ዛሬ ወር ድረስ ያለህበት ድረስ
ካልመጣው የለውም ማለት ነው..መቼም አልመጣም መቼም አታገኘኝም ማለት ነው…››
‹‹የማትረቢ ነሽ …..የሰው ስሜት መሰባበር የሚያስደስትሽ መጥፎ ሰው ነሽ….በይ አሁን
ስለሌላው ነገር መቀባጠርሽን አቁሚና የባንክ ቁጥርሽን ላኪልኝ..አንቺን ነው እንጂ ብርሽን
አልፈልግም….››ብስጭትጭት ..ንጭንጭ..እልኩባት
‹‹እንግዲያው የባንክ ደብተር የለኝም አልኩህ እኮ››
‹‹የሌላ ሰው ቢሆንም ላኪልኛ …ትቀልጂ.. ››
‹‹ካንተ በላይ የማምነው ሌላ ሰው የለኝም››
‹‹አትቀልጂ.. እኔ መጫወቻ አሻንጉሊትሽ አይደለውም….››
‹‹አውቃለው አይደለህም ..አንተ እስከዛሬ ካወቅኮቸውና ከቀረብኮቸው ሰዎች መካከል
በጣም የተለየህ ተወዳጅ ሰው ነህ….አንተ የህልሜ ወንድ ነህ…በህይወት ካለው ካንተ ርቄ
መኖር አልፈልግም….ሆዴ አንድ ወር ጠብቀኝ ..አንድ ወር ብቻ…..እስከዛ ካልመጣውልህ
ተስፋ ትቆርጥብኛለህ..እስከዛ ካልመጣውልህ ትረግመኛለህ..እስከዛ ካልመጣውልህ
ትጠላኛለህ…እስከዛ ካልመጣውልህ ትረሳኛለህ…››
‹‹…ሄሎ አንቺ ምን እያልሽ ነው....?ሄሎ ..ሄሎ እኮ ነው የምለው..?››ስልኩ
ተዘግቷል..መልሼ ደወልኩ ጥሪ አይቀበልም ይላል….
ምን እያለች ነው....?ምንስ እያደረገች ነው....?ከእኔ እና እሷ ግንኙነት የሚበልጥ ምን
አይነት የህይወት አላማ ቢኖራት ነው…..?ከሞት ወዲህ ማዶ እና ከሞት ወዲያ ማዶ
መሸጋገሪያ ድልድይ ላይ የሚያቆም ጉዳይ ምን አይነት ጉዳይ ቢሆን ነው....?ከመስመሩ
በቀኝ በኩል ከወደቅኩ በህይወት ስለምኖር ወደ አንተ እመጣለው..ከመስመሩ ወደግራ
ከወደቅኩ ደግሞ ወደ ሞት አለም የሚያደርስ ገደል ውስጥ ስለምሰምጥ መምጣት
አልችልም እለቺኝ እኮ ..አዎ ቀጥታ እንደዛ ነው ያለቺኝ..…ልክ በእሳት ተንቀልቅሎ
እንደሚንበለበል የመስቀል ደማራ ወደ ምዕራብ ወደቀ ወደ ምስራቅ እያልን አወዳደቁን
በማየት ትርጉሙን ለመተንበይ እንደምንጨነቅ ….ህልውናን ለእድል አደራ መስጠት…
አንደምንም መኪናዬን አስነሳውና ጉዞዬን ቀጠልኩ… ዋዩን አለፍኩ…ገበቴን በድን ሆኜ
ሰነጠኳት… ፊንጫአ ደረስኩ ..የፊንጫአ ከተማ እንኳን ደህና በጣችሁ ብላ እንግዶቾን
የምትቀበለው በአስፓልቷ ነው… ከጌዶ የጀመረው ኮረኮንች መንገድ ልክ ከተማዋ መግቢያ
ጋር ያበቃና አስፓልቱ ይጀምራል ከተማዋ ስታልቅ አስፓልቱም አብሮ ያልቃል..›
እኔ ግን እስፓልቱ ከማለቁ በፊት መኪናዬን አቆምኩና የባንክ ደብተሬን ይዤ መንገዱን
ተሸገሬ ወደ ንግድ ባንክ ገባው….አዎ ገንዘብ ማውጫ ፎርም ላይ 100 ሺ ብር ጻፍኩና
ፈርማዬን በጥንቃቄ ፈርሜ አዘጋጀው…ሌላ ገንዘብ መላኪያ ፎርም አወጣው…የባንክ ደብተር
ቁጥር ባትልክልኝም በስሟ መላክ እችላለው….የሷን ብራም ፍቅሯንም እኔ ጋር አኑሬ
በስቃይ ማቃተት አልፈልግም …. ቢያንስ ብሯን ትውስድልኝ…ስለዚህ በስሟ
እልክላታለው…፡፡
ቀን ጻፍኩ..የላኪ ስም በሚለው ክፍት ቦታ ላይ ሙሉ ስሜን ሞላው…የተቀባይ
ስም..ጂጂ..ተሳሳትኩ..ለካ እጅጋየው ነች….ግን እጅጋየው ማ…...?አላውቅም…የአባቷን
ስም አላውቅም..ምን አይነት ቀሺም ነኝ..ግን ይሄማ ቅሽምና አይደለም…ምን ጊዜ ኖሮኝ ገና
እሷን እንኳን በደንብ አውቄ መች ጨረስኩ …..?ለማንኛውም ስልኬን አወጣውና
ደወልኩላት..አሁንም ስልኳ ጥሪ አይቀበልም..ደገምኩት ተመሳሳይ ነው…የሞላውትን
ሁለቱንም ፎርም ጭምድድ አድርጌ የቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቅርጫት ውስጥ ወረወርኩና
ደብተሬን መልሼ ኪሴ ውስጥ በመክተት የባንክ ቤትቱ ግቢ ጥዬ ወጣው …ወደ መኪናዬ
ገባወና ነዳውት ….አሁን በቃኝ….. እንኳን ከእናንተ ጋር ከእራሴ ጋርም የማውራት አቅሙም
ሞራሉም የለኝም …
ይህቼ ልጅ መልሳ ወደ ህይወቴ ካልመጣች በስተቀር ከእናንተ ጋር መገናኘት
አልፈልግም…..ላወራችሁ ፍላጎቱም አቅሙም የለኝም..በቃኝ…ዝም ማለት ነው
የምፈልገው..ማሰብ ደክሞኛል..ማውራትም ደክሞኛል…
.
.
.
.
እንግዲህ ዋቅቶላ ጂጂ ዳግመኛ ወደ ህይወቴ እስካልተመለሰች ድረስ ምንም
አላወራችሁም ካለ ልናስገድደው አንችልም…ህገ መንግስቱም አይፈቅድልንም…ግን አንድ
ነገር አስቤያለው..ለምን ጂጂን እንከተላትም..እዛ አንቦ መነኸሪያ ጥለናት አይደል እሱን
ተከትለኝ ፊንጫአ ድረስ የመጣነው..እስኪ ደግሞ ወደ እሷ እንመለስና ታወራን እንደሆነ
እንሞክር….ከመቀመጫ ስነሳ.. ወደእሱ በፍጥነት ስራመድ… ጎንበስ ብዬ ጉንጩን ስስመው… ፊቴን
አዙሬ እና አንገቴን ደፍቼ ወደፊቴ ስርመድ..አስፓልቱን ተሸግሬ መነኸሪያ ግቢውስጥ
ስገባ..ይህን ሁሉ በብዥታ እና በደመነፍስ ነበር የከወንኩት….እዛ መቀመጫ ላይ ጥዬው
የመጣውት ሌላ ሰውን ሳይሆን የገዛ ግማሽ አካሌን እንደሆነ ነው የተሰማኝ..ነፍሴም
ስጋዬም ተገምሶ የቀረ…
ቋንቋ ድርጊትን በአግባቡ መግለፅ እና ማስረዳት ይችላል….ስሜትን ለመግለፅ ግን አቅም
ያንሰዋል…..፡፡ በፍፅም በቂ የሆነ አቅም አይኖረውም…በተለይ አንዳንድ ስሜቶችን ዛሬ እኔ
እንደተሰማኝ አይነት ስሜቶችን በትክክል አፍታቶና በታትኖ ለለማስረዳት ቃላቶች
ተሰባጥረው እና ተቀናብረው የሚፈጥሩት ዓረፍተ ነገር በቂ ሊሆን አይችልም….ዝም ብሎ
ሙከራ ነው..ላይ ላይን መዳከር…
...ወይኔ ጉዴ አንባዬ በጉንጬ ተንኳሎ እየወረደ ነው..ይሄ በጣም የሚገርም ነገር
ነው..ደግሞ የተለየ ለቅሶ ነው እያለቀስኩ ያለውት.. በአንድ አይኔ ብቻ ነው እንባዬ
የሚፈሰው…የአንድ አይኔ ምንጭ አሁንም እንደደረቀ ነው…..ቢሆንም ግን በአንድ አይኔም
ቢሆን እያለቀስኩ ነው…መነኸሪያ ውስጥ ገብቼ አጥር ጥግ ይዤ ድንጋይ ላይ ቁጭ
ብያለው….እንደዚህ ያደረግኩት አስቤበት አይደለም…ወደ አዲስአባ የሚሄደው ሚኒባስ
የትኛው እንደሆነ..? የት ጋር እንደምሳፈር…ወያላዎች ሲጣሩ ሰምቼም ሆነ ካፔላ አንብቤ
ወይንም ሌላ ሰው ጠይቄ ልሳፈር የምችልበት ሁኔታ ላይ አይደለውም…..ጆሮዎቼም
ተደፍነዋል አይኖቼም ታውረዋል….
እርግጥ ማታ የዘበራረቅኩት ነገር ትክክል እንዳልነበረ እየተሰማኝ ነው..አዎ
አጎጉቼዋለው…‹‹አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል›› ይባል የለ..በእንደእኔ አይነቱ ላይ
የተተረተ ነው…. እርግጥ በወቅቱ እኔም ተወዛግቤ ነበር…አንድ ልቤ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን
ተከትለሺው ሂጂ ሲለኝ… ሌላው ልቤ ደግሞ ወደ ፒያሳ ሲጎትተኝ ነበር፡፡
ይሄን ሰው በጣም ተሸንፌለተለው..ተሸንፌለታለው ስል አፍቅሬዋለው ለማለት አይደለም…
እርግጥ ለእሱ ለራሱ እንዳፈቀርኩት ነግሬዋለው…ልዋሸው ፈልጌ አይደለም..ግን ከፍቅር
የሚበልጥ ስሜት ነው ለእሱ እየተሰማኝ ያለው…ምን ማለቴ ነው…...? ከፍቅር የሚበልጥ
ስሜት ማለት ምን ማለት ነው…...?ምን አልባት ጥላቻ ካልሆነ በስተቀር…...?አንድ ሰውን
ማፍቀር ማለት ለዛ ሰው የሚሰማን በጣም የተጋነነ እና ጫፍ ድረስ የተለጠጠ መውደድ
ማለት ነው…..አዎ ያንን አውቃለው..እኔ ግን ለዚህ አይነት ስሜት የታደልኩ ሰው
አይደለውም…ይሄንን ስሜቴን ሮማን ድሮ.. ገና ድሮ ከማንነቴ ውስጥ ሰርዛዋለች….የቀረውን
እንጥፍጣፊ ስሜት ደግሞ ግብዝ እና ትምክህተኛ ወንዷችን ቀን በቀን ተፈራርቀው
አንጠፍጥፈው ደምስሰውታል፡፡
ዋቆቶላን ሳገኘው…ከእሱ ጋር ያሳለፍኳቸው ቀናት …በቃ ሰው እንደሆንኩ እንዳስብ ነው
ያደረገኝ….አባቴ ይመስለኛል..ታላቅ ወንድሜ ይመስለኛል..አጎቴም ይመስለኛል….ከእሱ ጋር
ስሆን በብዙ የስጋ ዘመዶቼ ተከብቤ ምፈነድቅ ይመስለኛል…ይሄን ደግሞ ለዘመናት ከፍቅር
በላይ ስራበው የኖርኩት ስሜት ነው….ለአንድ ሰው ምንም አይነት ዘመድ ኖሮት ካለማወቅ
በላይ ስቃይ የሚሆንበት ነገር የለም….እና ዋቅቶላን ሶስት ቀን ሙሉ ስከተለው የዋልኩት
የማንነቴ ክፋይ ነው ብዬ አስቤ ነው…ይሄንን ክፍተት የደፈነልኝ ስለመሰለኝ ነው…የሆነ
ለዘመናት ጠፍቶ በተአምር ያገኘውት ዘመዴ.. የቅርብ ስጋዬ ..ታላቅ ወንድሜ መስሎኝ
ነው…፡፡
ተከትዬው ላለመሄድ የወሰንኩት አሁን ቁጭ ብለን ቁርስ እየበላን ሳለ ሳይሆን ለሊቱን
ነው…ለሊት እሱ ደረት ላይ ተለጥፌ በእቅፉ ውስጥ ሆኜ አይኖቼን ጨለማው ላይ አፍጥጬ
ለሳዕታት ሳስብ ነበር…..የእሱ አቅፍ ማለት ለእኔ የእናት ማህፀን ማለት ነው….ሲያቅፈኝ
ፍጽም ደህንነት ፍጽም ሰላም ነው የሚሰማኝ…እናቴን ካጣው ቡኃላ ፍጽም ተሰምቶኝ
የማላውቀው አይነት ሰላም…አዎ ሁሉ ነገር እንዳዛ እንዳቀፍኩት ለዘላለም ቢቀጥል ምኜቴ
ነው.. ይሄንን በእሱ እቅፍ ውስጥ የማገኘውን ደስታ ላለማጣት ስል ገነት እንኳን የእኔ
ብትሆን መተው እችላለው…አዎ ምንም ሳላቅማማ እተዋታለው…፡፡ግን በቀሌን ልተው
አልችልም..ፈጽሞ ሮማንን ለማጥፋት ለወራት የነደፍኩትን እቅድ መሰረዝ አልችልም….ለዛ
ነው ጥዬው ለመመለስ የወሰንኩት..አትፍረዱብኝ ፡፡ ይሄ በቀል ለእኔ ከገዛ ህይወቴ በላይ
ዋጋ አለው….፡፡ይሄንን ደግሞ ለእሱ ላስረዳው አልችልም..እንዴት አድርጌ..?፡፡ ስለዚህ
ዝም ብዬው መሄድ ነበር ያለብኝ ….ያደረግኩትም እንደዛው ነው….፡፡
ከአንድ ሰዓት ቡኃላ ይመስለኛል…አዲስአባ አዲስአባ የሚል የጥሪ ድምጽ በጆሮዬ ገባ…
የድንጋይ መቀመጫውን ትቼ ተነሳው..መንቀሳቀስ ግን አልቻልኩም..እግሬ አብጦ ዝሆኔ
የነፋፋው ይመስል ያበጠ መሰለኝ..ከእግሬም አልፎ ጭንቅላቴ ድረስ ነው ብዥ ያለብኝ….
ከድንዛዜዬ ለማገገም 5 የሚሆኑ ደቂቆችን ከቆምኩበት ሳልንቀሳቀስ ማበከን የግድ ብሎኝ
ነበር..ከዛ ቀስ በቀስ እያለማመድኩ ወደ ሚኒባሱ ተራመድኩና ተሳፈርኩ…..ሚኒባሱ
እስኪሞላ ሃያ ደቂቃ ቆየን…
ይሄኔ ሄዶ ይሆን .. ..?ምን ተሰማቶት ይሆን…..?ልደውልለት ይሆን…..?ከአምስት ጊዜ
በላይ ስልኬን ለመደወል አመቻችቼ ነበር.. ላደርገው ግን አቅም አልነበረኝም…፡፡
አንቦን ለቀን ወጣን ቡራዩ ልደርስ 25 ኪሎ ሜትር ያህል ሲቀረኝ ነበር ስልኬ የጠራው…
….እሱ ነው የደወለው ..አዎ እሱ ነው ..ምን ማድረግ አለብኝ....?ዝም ልበለው....?
ላንሳው...?.ነፍስና ስጋዬ ነው የተላቀቀው…..ግን አነሳውት….
…..እሱባለው የእቁብን መቶ ሺ ብር በእሱ ደብተር እንዳስገባ ሊነግረኝ ነው
የደወለልኝ…..እና ያ በመሆኑ ደግሞ ከገመትኩትም በላይ አበሳጭቶታል…..የላኩለትን ብር
መልሼ እንድወስድለት ፈልጎል….መጨረሻ በስድብና በእርግማን ሲያንቧርቅብኝ
ድንጋጤውን መቋቋም አልቻልኩም… ጠረቀምኩት…. በፍጥነት መለሶ ሳይደውልልኝ በፊት
ሙሉ በሙሉ ስዊች ኦፍ አደረግኩት..
ምንድነው የሰራውት…...?ወራጅ ሁሉ ማለት አምሮኝ ነበር..እርግጠኛ ነኝ እራሴ የምነዳው
የግል መኪናዬ ቢሆን ኖሮ በዚህ ሰዓት ምንም ሳላቅማማ ወደ ኃላ ተመልሼ ወደ እሱ እበር
ነበር …አዎ በርሬ እሄድና ጉያው ውስጥ ሽጉጥ ብዬ ለሳዕታት ፀጥ ብዬ የሰላም እንቀልፍ
እተኛ ነበር…ግን አሁን ምንም ማድረግ አልችልም… ወራጅ ብዬ ብወርድ ወደኃላም ሆነ ወደ
ፊት መጓዝ አልችልም..ወደ ሁለቱም አቅጣጫ ትራንስፖርት ማግኘት አልችልም…አውላላ
ሜዳ ነው….በእግርም የማይሞከር ነው..ስለዚህ ያለኝ አንድ ምርጫ ስሜቴን ዋጥ ማድረግ
ነው…ማፈን..፡፡የታፈነ ነገር ደግሞ ይቆያል እንጂ መፈንዳቱ አይቀር …እና
እንዳልፈነዳላችሁ፡፡
የተሳፈርኩበት ሚኒባስ አስኮ መነኸሪያ ወስዶ ጣለኝ …..ቀጥታ ወደ ፍል ውሀ ነው
የሄድኩት… ሰውነቴ ሲጠራ እና ሲነቃቃ ውስጤም ይፍታታልኛል ብዬ በማሰብ…አስከ12
ሰዓት እዛው ቆየው…አዎ ያሰብኩትን ያህል ባይሆንም በተወሰነ መልኩ ተረጋግቼያለው..
ግን ፈልውሀን ለቅቄ ወደፒያሳ መንገዴን ስቀጥል.. በሩቅ ያየውት ሰው ሁሉ ዋቅቶላን
እየመሰለኝ ጠርቼ ላስቆመው ሮጬ ልይዘው እፈልጋለው…እንዴት አንድ ሰው ሌላ ሰውን
እንደዚህ ይርባል…..?በፊት ‹
ሰው ራበኝ› ሲሉ ስሰማ ማጋነን ይመስለኝ ነበር…ለካ ሰውን
መራብ ከምግብ በላይ ነው ስጋንም መንፈስንም የሚያደክመው…ወደ ቤቴ አይደለም
የሄድኩት…
አሁን ጋሼን ማግኘት አለብኝ ..ከዚህ ቁዘማ ውስጥ ሊያወጣኝ የሚችለው የጋሼ ምክር ብቻ
ነው፡፡
ደረስኩና ገርበብ ያለደረስኩና ገርበብ ያለውን የቤቱን በራፍ ገፋ አደረግኩት… ሲጢጢ አለና ተከፈተልኝ..ሹልክ
ብዬ ገባው…ጋሼ አልጋው ላይ ጋደም ብለው መፃሀፍ ቅዱስ ያነባል…አይኛቸውን ወደ በራፍ
ሲመልሱ ተመለከቱኝ…ያ የተሸበበ ጨምዳዳ የሽማጊሌ ፊታቸው እየተላቀቀ… እየፈገገ
ሲደምቅ ታየኝ… ሲያነቡ የነበረውን መፃፋ አጥፎ ከመኝታቸው ቀና ብለው ተነሱ….››
‹‹አንቺ ወፍ የት አባሽ ጠፍተሸ ነበር...?ደግሞ አለባበስሽ ..ፐ..ፐ..ፐ እንዴት አባቱ ነው
ሚያምርብሽ…..?››
ምንም አልመለስኩለትም..አካባቢዬ ያገኘውትን ኩርሲ ያዝኩና ወደ እሳቸው ተራመድኩ…
ውሪዎቹ እቤት ባለመኖራቸው በጣም ነው ደስ ያለኝ….ኩርሲውን ወደ ራስጌው አስጠግቼ
አስቀመጥኩትና ተቀመጥኩበት ..አንገቴን አቀርቅሬ ዝም አልኩ….
‹‹ማን አባቱ ነው ..የእኔን ወፍ እንዲህ ያስከፋት..?››ጎተቱኝና ታፋቸው ላይ አስተኙኝ…
በእድሜ የጠነከረ ቆርፋዳ እጃቸውን ጭንቅላቴ ላይ አሳርፈው በፊቱም ተተረማምሶ
የነበረው ፀጉሬን ይበልጥ ያተረማምሱት ጀመር..እንዲህ ሲያደርጉ ደስ ይለኛል…በቃ ሁሌ
ሲከፋኝ ወደ እሳቸው የምሮጠው እንዲመክሩኝ ወይም እንዲያፅናኑኝ ብቻ አይደለም…
እንደውም ከዛ በላይ እንዲህ እንዲዳብሱኝ ነው የምፈልገው..ይሄ እናቴን ያስታውሰኛል…
በህይወት ሳለች እናቴ ከምታደርጋቸው ነገሮች መካከል ዋናው ይሄ ነው… ሲከፋኝ ወይም
ሲያመኝ ጭንቅላቴን በመዳበስ ማረጋጋት..ማባበል…ማስተኛት..
‹‹የእኔ ወፍ እንዲህ አምሮብሽ… እንዲህ ሴት መስለሽ ልትስቂና ልትደሰቺ ሲገባሽ
ምንድነው ሚያስከፋሽ…..?የእኔ ጀግና አንቺ እንዲህ ስትሸበሪ ማየት ጭራሽ ያስረጀኛል
ታውቂያለሽ አይደል…..?እኔ እንደውም ይሄን ሶስት ቀን ከአይኔ ስትጠፊብኝ ሰግቼ እኮ
ቢቸግረኝ ልጆቹን ተበትነው እንዲፈልጉሽ አዝዤቸው ነው …አንቺ እኮ ለእኔ ፒያሳዬ
ነሽ..ፒያሳን የሚያደምቅልኝ የሰው ትርምስ ወይም የሙዚቃው ጩኸት አይደለም…ያነቺ
በውስጦ መኖር ነው፡፡
እጆቻቸው በፀጉሬ ውስጥ እየተርመሰመሰ ጭንቅላቴን እየደባበሱ ያወራሉ..ሲያወሩኝ ዝም
ብለው ነው…መልስ እንድሰጣቸው ሳይሆን ዝም ብዬ እንዳዳምጣቸው ነው…
‹‹…..ልጄ ያቺ ከይሲ ተተናኮለቺሽ እንዴ…...?እንዴ አንቺ..!!!››ደንግጠው ቀና
አደረጉኝ….አትኩረው አዩኝ..ልክ እንደጥዋቱ አሁንም እንባዬ በአንድ ጉንጬ
ይፈሳል..ጎትተው አስነሱኝና አልጋቸው ላይ ከጎናቸው አስቀመጡኝ…አቅፈው ጉያቸው ውስጥ
ከተቱኝ…
ልጄ በራስሽ አትጨክኚበት…ግድ የለም እስቲ ለስሜትሽ ተሸነፊ….በእኛ ማህበረሰብ
ውስጥ ለስሜት መሸነፍ ደካማ ነት ነው…ለስሜት ስትሸነፊ ለሀጥያት እንደተሸነፍሽ ነው
የሚቆጠረው..ግን ግዴለሽም በእኔ ይሁንብሽ ለስሜት መሸነፍ ሰዋዊነት ነው….እንባሽን
አትገድቢው…ድምጽ አውጥተሸ አልቅሺ …ተንሰቅስቀሽ አልቅሺ..በአንድ አይንሽ ሳይሆን
በሁለቱም አይኖችሽ እንባሽ ይፍሰስ…ለዚህ እንዲረዳሽ ያበሳጨሽን ሰው ያደረገሽን ነገር
አስቢ..ያጣሻትን እናትሽንም አስቢ …ያም ካልበቃሽ ያቺን መሰሪ በህይወትሽን እንዴት
ስትጫወትብሽ እንደኖረች አስቢ…….››ጋሼ መሰሪ ብለው ሚጠሩት ሮማንን ነው..ከበፊትም
ጀመረው ስሟን መጥራት ይቀፋቸዋል..
የማላውቀው ኃይል ከልቤ ተቦጭቆ ተነሳ …ልቆጣጠረው የማልችለው እሳተ ጎመራ
ከውስጤ ፈነዳ… ድምጽ ከጉሮሮዬ እየተምዘገዘገ መውጣት ጀመረ…. እንባዬ በሁለቱም
አይኖቼ በሁለቱም ጉንጮቼ ይወርድ ጀመር..አዎ ያጋተው የስሜቴ ደመና ከውስጥ በፈነዳው
ኃይል ተበታተነ..የራሴን ድምጽ የራሴን መንሰቅሰቅ እራሴው አዳምጠው ጀመር …
ህእ..ህእ..ህእ……ህእ….
ጋሼ ዜና እያባበሉኝ አይደለም…እያወሩልኝም አይደለም..ብቻ እንዳቀፍኝ ነው…ብቻ
ጭንቅላቴን እየደበሱኝ ነው….
በተተረማመሰ ሁኔታ በራፉ ተከፈተ…
‹‹ጋሼ የለችም..››
‹‹ጋሼ አጣናት…››
‹‹እኔም አላገኘዋትም…››
ሁሉም በተሰማሩበት ተልዕኮ እንዳልተሳካላቸው እየተናገሩ ጋሼ ፊት ሲቆሙ …እኔን ጋሼ
ጉያ ውስጥ ኩርምት ብዬ ሌላ ሰው መስዬ(ቀሚስ ለብሼ አይተውኝ
ስለማያውቁ)ሲመለከቱኝ …በደስታ ተውጠው….
‹‹መጥታለች..››
‹‹እቺውና….››
ተራ በተራ እየትንደረደሩ እላዬ ላይ ተንጠለጠሉብኝ
‹‹..ቀስ ቀስ..አረ ገደላችዋት››ጋሼ ናቸው እየተከላከሉልኝ ያሉት..እኔም እንባዬን እንዳያዩ
በዘዴ እየጣራረግኩ ሁሉንም በየተራ ሳምኳቸው….
‹‹የት ጠፍተሸ ነው..?››
‹‹ፖሊስ ጣቢያ ሁሉ ጠየቅን እኮ››
‹‹እያለቀስን ነበር እኮ››
‹‹የት ተደብቀሽ ነው..?››
‹‹ለምን ቀሚስ አደረግሽ..?››
ሁሉም ያለመጣባበቅ እና ያለመደማመጥ የተሰማውን ያወራታል….፡፡አለው….ይሄው
መጣው አይደል…
‹‹ሁለተኛ ሳትነግሪን እንዳትጠፊ..››
‹‹አሺ አላደርገውም…አሁን እራት በላታችሆል....?››አልኳቸው… ከጭቅጭቃቸው
ለመገላገል
‹‹አይ አንቺን ስንፈልግ ነበር ..››
‹‹ስለዚህ እራት አምጡና አብረን እንባላ… ››በማለት ቦርሳዬን አወጣውና ሁለት መቶ ብር
አውጥቼ ሰጣዋቸው‹‹..ደስ ያላችሁን ምግብ ገዝታችሁ ኑ››
የሰጠዋቸውን ብር ተቀብለው ግር ብለው እንደገቡ ግር ብለው በደስታ እየተንጫጩ ወጡ…
‹‹ልጄ አየሽ አይደል እንዴት እንደሚወዱሽ…...?እራት በላችሁ ወይ ብለሽ ጠየቅሻቸው
አይደል…..?እራት ሳይሆን ምሳቸውን አልበሉም..ቀኑን ሙሉ አንቺን በመፈለግ ሲንከራተቱ
ነው የዋሉት…ሁላችንም በጣም ነው የምንወድሽ….አንቺም ትወጂናለሽ አውቃለው..፡፡ግን
እኛን ብቻ ሳይሆን ሌላ ሰውም ለመውደድ ሞክሪ…ቅድም እንደነገርኩሽ ለስሜትሽ መሸነፍን
ተማሪ….ስሜትሽ ውደጂ ካለሽ ውደጂ…..››
ደነገጥኩ… ጋሼ ምንድነው የሚያወሩት....?የምን መውደድ ነው....?ስለዋቅቶላ
ነግሬቸዋለው እንዴ....?ከእቅፉቸው ወጣውና አትኩሬ አየዋቸው… ጥያቄያዊ አስተያየት….
‹‹አዎ ገብቶኛል….እኔ እናትሽ እቅፍ ሆነሽ ጡት ከምትጠቢበት ጊዜ ጀምሮ
አውቅሻለው..አንቺ ማለት ለእኔ ልጄ ነሽ…. አባት ደግሞ የልጁን እያንዳንዱን የስሜት
ለውጥ ያስተውላል..ዛሬ ደሰ ብሎኛል… በአንቺ ላይ ባየውት የስሜት ለውጥ ደስተኛ ነኝ…››
‹‹እንዴ ጋሼ ስለከፋኝ ነው ደስ ያሚሎት....?ስላለቀስኩ ነው የተደሰቱት..?››
‹‹አዎ …በተለይ ስላለቀሽ ደስ ብሎኛል..ይሄ በአንቺ ህይወት አዲስ ባህሪ ነው …አዲስ
ባህሪ ደግሞ ሚወለደው በህይወት ውስጥ አዲስ ነገር ሲከሰት ነው..እርግጠኛ ነኝ አንድ
ሸጋ የልብሽ ደጃፍ ላይ ቆሞ እያንኳኳ ነው… አንቺ ደግሞ ያን በር መክፈት መሸነፍ አድርገሽ
ስለወሰድሽው እየገፋሽው ነው…ልብሽና አዕምሮሽ ጦርነት ገጥመዋል…..››
‹‹አረ ጋሼ እንደዛ አይደለም..››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው..?››ሽማጊሌው በአባታዊ ትዝብት ጠየቁኝ
‹እርግጥ በጣም ጥሩ ሰው ነው…ግን በቃ ወንድሜ እንዲሆን ነው የምፈልገው… ታላቅ
ወንድሜ…ከእሱ ጋር መኖር ከእሱ ጋር ማደር እፈልጋለው..ግን እህቱ ሆኜ ….እንደዛ ነው
የምፈልገው..ያንን ማድረግ ስላልቻልኩ ነው የከፋኝ››
‹‹ፈገግ አሉ ጋሼ.. ይህቺን አይነት የጋሼን ፈገግታን አቃታለው…የነገር ፈገግታ ነች…
የምታወሪውን ነገር አላመንኩሽም የሚል መልዕክት አላት…የምታወሪውን ወንድ ከመውደድ
በላይ አፍቅረሽዋል እያለኝ ነው..ይሄንን ከሳቃቸው ተረድቼያለው››
‹‹ጋሼ እርሶ ደግሞ የውስጤን ከእኔ በላይ ያውቃሉ እንዴ…...?ጋሼ እኔ ልሙት እወነቴን ነው
አላፈቀርኩትም..ስታስበው እኔ...፡

በማግስቱ በጥዋት ነው ከጋሼ የተለየውት … ቀጥታ ወደ ስራዬ ነው የገባውት…ምንም
የሚባክን ጊዜ የለኝም…አዎ ጊዜ የለኝም…ቁርጤን ማወቅ አለብኝ፡፡አላማዬን ለማሳካት
ሶስት ሰዎችን መርጬያለው… ሶስት የልብ ጓደኛቼን ..በጣም የማምናቸውን እና
ህይወታቸውን ጭምር ብጠይቃቸው እንደማይከለክሉኝ የማምንባቸውን፡፡ይህንን ስል መቼስ
አይገባችሁም …የአንቺ ጓደኞች ማን የሚሏቸው ክርስቶስ ናቸው ለሰው ሲሉ ህይወታቸውን
የሚሰጡት…? ትሉኝ ይሆናል..፡፡ተሳስተሸል..ወይም ጓደኞችሽን በተመለከተ ያለሽ ግንዛቤ
የተጋነነ ነው ብላችሁም ምክር ልትለግሱኝ ትቃጡ ይሆናል፡፡ይሄንን ለእናንተ በማስረዳት
ላሳምናችሁ አልችልም…ማሳመንም አይጠቀበቅብኝም..እኔ ግን እንደዛ ነው የሚሰማኝ…ያ
ደግሞ በቂ ነው፡፡
..ለማኛውም እነዚህን ጓደኞቼን በመጠኑ ላስተዋውቃችሁ… ሶስቱም ሌቦች ናቸው፡፡
ስራቸውን ልብነት ነው ልላችሁ ፈልጌ ነው..ያው መተዳደሪያ ከሆነ መኪና ማጠብም ኪስ
ማጠብም ስራ ነው..ዋናው ገንዘብ ማስገኘቱ አይደል…ምነው ተሳሳትኩ እንዴ…? ሶስቱ
ሌቦች ሁለት ወንዶችና አንዷ ሴት ነች…እነዚህ ሶስት ሌቦች ዕድሜያቸው ያው ከ19-23
ይሆናል… ግምት ነው…፡፡ትውውቃቸውም ያው ከዕድሜያቸው ጋር ተቀራራቢ ነው…፡፡ይሄንን
ስላችሁ አንድ ቤት ነው እንዴ ያደጉት…? ወይም የአንድ ሰው ልጆች ይሆኑ እንዴ…?
ብላችሁ በውስጣችሁ ጥያቄ ማንሳታችሁ አይቀርም … ብዙም አልተሳሳታችሁም…አንድ
ቤት ባይሆንም አንድ በረንዳ ላይ አንድ ጆንያ እየተናጠቁ በመልብስ..አንድ ቂጣ ለሶስት
በጣጥቀው በመቃመስ …አጫሽ የጣለውን አንድ የሲጋራ ቁሩ ተቀባብለው በማጬስ…
ከጫት ቤት የተሰበሰበ ገራባ አንድ ላይ ተከፋሎ በመቃምና በመመርቀን…ከአንድ መኪና
በአንድ ትንፋሽ ቤንዚል በመሳብ ክፉውንም ደጉንም አብረው ያሳለፉ በአንድ ቤት ሳይሆን
በአንድ ልብ የሚኖሩ ልጆች በሏቸው..እርግጥ ሶስቱም በተለያዩ እናቶች ተፀንሰው
በተቀራራቢ ጊዜ ተቀራራቢ ቦታ ተወልደው በተለያየ ምክንያት እናቶቻውን ያጡ ፒያሳዊያን
ናቸው…..
….ሁለቱ ወንዶች አቃሟቸው ፍፅም ተቀራኒ ነው፡፡አንዱን ስንዝሮ እንለዋለን….ብጭጭ ያለ
ቀይ..አጭር…ቀጭን..ተንኮለኛ እና ለፍላፊ ነው፡፡ሌላኛው ዋርካ ብለን ነው የምንጠራው ...
ግዙፍ ነው..ረጂም ጥቁር…ዝግ ..ቢኮረኩሩትም የማይስቅ… የአፉ ስፋት ስንዝሮን
ጠቅልለው ቢያጎርሱት ሳያላምጥ ዋጥ ማድረግ የሚችል አይነት ተፈጥሮ ያለው ነው…
ትግስተኛና እርግታ የተላበሰ ነው..ግን የትግስቱ ጫፍ ላይ ከደረሰ በቃ አስር ሰው
አይመልሰውም….የቆሰለ ጎሽ በሉት….ፊት ለፊት ያገኘውን ሁሉ በመደረማመስ ከገደል
ሚደበላልቅ…
እንዲህ ተቃራኒ ባህሪ ያላቸው ሁለቱ ጓደኛሞች ግን የእወነት መንትያ ነው የሚመስሉት
..አንዱ ሳይናገር ሌላው ምን እንዳሰበ በቀላሉ ያውቃል…አንዱ ካንዱ ውጭ መኖር ፈጽሞ
አያስብም …እድሜ ልካቸውን የግል የሚባል ነገር የላቸወም..ህፃን ሆነው ውሻ ሲያሳድጉ
ራሱ ውሻው የጋራቸው ነበር….ፀባቸው የጋራ ነው ፍቅራቸውም የጋራ ነው፡፡በአንዱ
ሚወደደድ ሰው በሌላውም በተመሳሳይ መጠን ይወደዳል…በአንደኛው ቂም የተያዘበት
ሌለኛው ነው የሚበቀለው….ሌላው ይቅር ህመማቸው እንኳን የጋራ ነው…ልክ ከአንድ
እንቁላል ተከፍሎ እንደተሰራ እና ከአንድ ማህፀን በአንደ ጊዜ እንደወጣ የእውነት
ተፈጥሮአዊ መንታ አንዱ ከታመመ ከሳዕታት ቡኃላ ሌላውም ያታመማል….
ይሄ ሁሉ ስለእነሱ በቅርብ በሚያውቁ ሰዎች በገረሜታና በአድናቆት ሚያወሩላቸው
ታሪካቸው ነው…ግን ከዛም ከፍ ያለ ታሪክ አላቸው …ከኩኩሻ ጋር የሚያያዝ ታሪክ…ኩኩሻ
ሶስተኛዋ መንትያ ወይም ሴቷ ነች ..ሶስተኛዋ ተጣማሪያቸው ..ውሪ ህጻን ሳሉ ማንም
እንዳይተናኮላት ከህብረታቸው ቀላቀሏት..አብራቸው መኖር አብራቸው መተኛት
ጀመረች..ሰው እንዳይተናኮላት ወይም እንዳትፈራባቸው መሀከላቸው ነበር
የሚያስተኞት….እዛ ጎዳና ላይ ከኩታራነት እድሜያቸው ጀምሮ መሀከል አድርገዋት ግራና
ቀኞ ሲተኙ ከጥቃትም ከብርድም ነበር የሚከላከሉላት…እኩል እያጎረሷት እኩል እየጠበቋት
..እኩል እየተንከባከቧት አብራቸው አደገች…እኩል አደጉ..ለአቅመ መዳራትም እኩል
ደረሱ….የትኛው አጋጣሚ እና በምን ሁኔታ እንደሆነ አላውቅም ሁለቱም በእኩል ጊዜ
ከኩኩሻ ፍቅር ያዛቸው..…እኩል ጠየቋት..እሷም እኩል ተቀበለቻቸው..፡፡
ይለይልን ብለው አልተደባደቡም…የግሌ ነች ብለው አልተፈነካከቱም…ከሁለታችን አንዳችንን
ምረጪ ብለው ፈተና ውስጥ አላስገቧትም…በደስታ ፍቅራቸውን ቀጠሉ…
ይሄው አምስት አመት አስቆጥሯል ኩክሻ የስንዝሮ እና የዋርካው ሚስት
ከሆነች….የአንደኛው ደረት ላይ ተለጥፋ የአንደኛውን ከንፈር ስትስም ለሚመለከት ሰው
ፊልም እየሰሩ እንጂ የእውነት ህይወት አይመስልም…
የሚገርመው ኩክሻ እንደስንዝሮም ያላጠረች እንደዋርካውም ያረዘመች መሀከለኛ ቁመት
ያላት የጠይም ቆንጆ ሴት ነች… እና ሶስቱ አብረው ሲሄዱ ያስቃሉ..ብዙ ጊዜ እሷን
መሀከላቸው አድርገዋት ነው የሚሄዱት ልክ እንደልጅነታቸው እና ስታወራቸው ስንዝሮ
ወደላይ አንጋጦ ሲያዳምጣት ዋርካው ደግሞ ወደታች አዘግዝቆ ይሰማታል…ይሄም
ለተመልካች ፈገግ ያሰኛል፡፡
በነገራችን ላይ አሁን በረንዳ አይደለም የሚኖሩት ከበረንዳ ህይወት ከተላቀቁ ቢያንስ 7
አመት ይሆናቸዋል…አዋሬ አካባቢ ሁለት ክፍል ቤት ተከራይተው ይኖራሉ…ሁለት ክፍል ቤት
ስላችሁ መቼስ በአዕምሮችሁ ሁለቱም ክፍል ላይ አንድ አንድ አልጋ ተዘርግቶ አንዱ
የአንደኛው ሌላው ክፍል የሌላው ….፡፡እንደዛማ አይደረግም…አንደኛው መኝታ ቤት አንደኛው
ሳሎን ነው..አልጋቸው አንድ ብቻ ሆኖ ባለሜትር ከሰማንያ ሲሆን ሶስቱም የሚተኙት አንድ
አልጋ ላይ ነው…እስር ቤት ገብተው በመንግስት ቁጥጥር ስር የመሆን አጋጣሚ ካልተፈጠረ
በስተቀር አንደኛው ከአንደኛው ተለይቶ መተኛት የማይታሰብ ነው…ሲተኙ እሷን መሀል
አድርገው ነው….
በነገራችን ላይ ከሁለት አመት በፊት ወልዳላቸው ነበር…ምታምር እራሷን የምትመስል ሴት
ልጅ …አቤት እንዴት ይወዷት እንደነበር…አንዱ ሰውነቷን ሲያጥባት አንዱ ዳይፐር
ይቀይርላት ነበር..አንዱ ሲመግባት አንዱ ያጫውታታል….ክፋቱ ከስድስት ወር በላይ በምድር
እንድትቆይ አልተፈቀደላትም ነበር ..ድንገት ተቀጨችባቸው..ከእናትዬው በላይ ያዘኑት ሁለቱ
አባቶች ናቸው….አንድ የጋራ ልጃቸውን ነበር ያጡት…ከዛ ቡኃላ ግን እንዴት ደግማ
እንዳላረገዘችላቸው አላውቅም…እኔም ሀዘናቸውን መቀስቀስ ይሆናል ብዬ ስለሰብኩ
ጠይቄያቸው አላውቅም…ለማንኛውም የእኔ ጓደኞች እንዲህ አይነት ናቸው….ብዙ ብዙ ታሪክ
አብረን አሳልፈናል..ክፍውንም ደጉንም…ሌባ በነበርኩበት ጊዜም አብዛኛውን ስራዬን
ከእነሱጋር በቅንጅት ነበር የምሰራው…እወዳቸዋለው ይወዱኛል….
ዛሬ ለከባድ ተልዕኮ ጠረቼያቸዋለው..ለምን እንደፈልግኮቸው ስነግራቸው ያለምንም
ማንገራገር ሶስቱም በአንድ ድምጽ ተስማምተው ነው የመጡት….እነዚህ ጓደኞቼ ያው ጨዋ
ከሚባለው ማህበረስብ ሚለዩበት ነገር አላቸው….አሪፍ ፕሮፌሽናል ሌባን አምነህ አንድ
ሻንጣ ብር ብትሰጠው አትጠራጠር አድርስ ያልከው ቦታ አንድ ነጠላ ብር እንኳን ከላዩ ላይ ሳይቆነጥር ያደርሰልሀል…ህይወትህንም አደራ ከሰጠሀው ህይወቱን ሰጥቶ ይጠብቅልሀል…
ለዛ ነው እንዲህ በእነሱ ላይ የተማመንኩት….
አራት በአራት በሆነችው በእኔ ክፍል ውስጥ ነው ያለነው…እያንዳንዳችን አንድ አንድ ዙርባ
በለጬ ይዘናል….ከእኔ በስተቀር ሁሉም ኒያላቸውን እያቦነኑት ነው…እቤቷ ታፍናለች…እኔ
እራሴ ምርቅን ቅን ብያለው…ጫት ስቅም ከአምስት ቀን ቡኃላ ነው …ዕድሜ ለዛ ዋቅቶላ
ለተባለው ሰው… ከእሱ ጋር በሆንኩበት ጊዜ እኮ ሁሉን ነገር ትቼውና እረስቼው ነበር…
አይደለም ለመቃም ጫት ሚባል ነገር እንኳን መኖሩን ትዝ ብሎኝ አያውቅም ነበር…አይ የኔ
ነገር..ሰበብ ፈልጌ አስታወስኩት አይደል…?ምን ላድረግ ወድጄም አይደለ…በነገራችን ላይ
አሁን ጓደኞቼ ከመምጣታቸው ከአንድ ሰዓት በፊት ደውዬለት ነበር..እንዲህ ነበር የስልክ
ልውውጡ
‹‹ሄሎ ዋቅቶላ››
‹‹ሄሎ ..ደህና ነሽ…ላክሺልኝ››አለኝ ….ከዚህ ጥያቄ ይልቅ ሞቅ ያለ ሰላምታ ነበር
የጠበቅኩት…
‹‹ምኑን…?››
‹‹የባንክ ቁጥሩን..››
‹‹አንተ መቶ ሺብር ብርቅህ እው እንዴ .. …?እኔ እኮ ሰላም ልልህ ነው
የደወልኩት››ተንዘረዘርኩበት
‹‹ያንቺ ሰላምታ ከራስ ምታቴ ይፈውሰኛል……?ሰላምታሽ ናፍቆቴን ያስታግስልኛል….…?
ሰላምታ..ሰላምታ ››
‹‹አረ አረጋጋው››
‹‹አልረጋጋም ..ምንም ልረጋጋ አልችልም››
‹‹እና ምን ይሁን…?››ተበሳጨው..በጣም አበሳጨኝ
‹‹ምን ይሁን .. …?ነያ..መጣለው ብለሽ አልነበር …?ነይ..አብሬህ እኖራለው ብለሺኝ
አልነበር ነይና አብረን እንኑር››
‹‹አንድ ወር ጠብቀኝ ብዬአለው እኮ….…?››
‹‹አንድ ወር ማለት እኮ …. ቆይ ከተለየውሽ ስንት ቀን ሆነው…?.››
.‹‹አንድ ቀን››
‹‹እና ይሄ አንድ ቀን ምን ያህል ረጂምምምምምምመም እንደሆነ ታውቂያለሽ……?
አታውቂም….30 ቀን ማለት ደግሞ እስካአሁን ያሳለፍኩትን ጣር እና መከራ 30 ጊዜ እጥፍ
ማለት ነው…፡፡ታዲያ አስበሽዋል..…?ይሄንንማ አልችልም..ልጠብቅሽ አልችልም…፡፡ዛሬውኑ
ወይም ነገ ማትመጪ ከሆነ ልጠብቅሽ አልችልም..ካልሆነ አንቺን ከመጠበቅ መርሳት
መሞከሩ ይሻለኛል…››
‹‹ልመጣማ አልችልም..ጉዳዬን ሳልጨርስ ልመጣ አልችልም››
‹‹እሺ አንቺ ካልቻልስ እኔ ልምጣ…?››አለኝ በተሰባበረ እና በተቆራረጠ ድምጽ
‹‹ወደ የት…?››ሌላ ድንጋጤ
‹‹አንቺ ጋር ነዋ››
‹‹ልጅህስ…?››
x

ለመጀመሪያ ጊዜ እንዳየዋት ሁሉ ፍዝዝዝ ነው ያልኩት…..በጣም ነው የምታምረው…

Popular Posts

© የፍቅር ቀጠሮ የፍቅር ታሪክ 2020
Maira Gall